TZTA - October 2012 Publication

Page 1

ADDRESS: 851 Bloor St.W. Toronto, ON M6G 1M3, Canada / Tel.: 416-653-3839 / Cell: 416-898-1353 / Fax: 416-653-3413 / E- mail: tzta@sympatico.ca / Website: www.tzta.ca THIS ISSUE: VOLUME XVII, NO. 10: October 23, 2012 / NEXT ISSUE: TUESDAY, November 20, 2012 / ADVERTISEMENT & DEADLINE: November 13, 2012

2

አዲሱ ቤተክርስቲያን ሕንጻ በቶሮንቶ November 17 and November 18, 2012

ለማንኛውም ማስታወቂያ For Advertisement call @ 416-898-1353 Email:- tzta@sympatico.ca

ሊመርቅ ነው። BLACk LION HAIR SALON & BARBER SHOP/Beauty Supply

ማይክ

Tel.:- 416-536-2394 Cell:- 647-893-2208

M I C

E-mail:- michaelzewge@hotmail.com

ይህ አዲሱ ቤተ ክርስቲያን በሚመጣው ኖቬምበር 17 ቀንና ኖቨምበር 18 ቀን 2012 ዓ.ም. በታላቅ ክብር ሊመርቅ በመሆኑ የትዝታ ጋዜጣ አዘጋጅ ይህን ምክንያት በማደረግ ከዋናው አስተዳዳሪ ከሊቀ ካህናት ምሳሌ ጋር ያደረገውን ቃለ መጠይቅ...ገጽ/5 ይመልከቱ

አዲሱ ቤተክርስቲያን ሕንጻ

Address by Minister Baird at Inter-Parliamentary Union Assembly As we stand on the threshold of the next century, we are reminded of that old adage, “the only constant is change.” When change is swift and unexpected, it is all the more important that we focus on the constant that remains true: that people everywhere will fight for dignity. The dignity to live in freedom. The dignity to live in peace. The dignity to provide for one’s family. In the current and raging storm of change, societies that are free, open and democratic stand as beacons of light. We know what it takes to build the conditions in which people live with the dignity they crave. We know that freedom, democracy and human rights are the values upon which pluralistic societies are built. But we also know that pluralism will not flourish unless we embrace the diversity of our societies. As Michel de Montaigne said, “there never were in the world two opinions alike, no more than two hairs or two grains; the most universal quality is diversity.” Read more/19

Minister Baird Global Immigration Services ግሎባል ኢሚግሬሽን አገልግሎት

TORONTO VARIETY STORE

Toronto, ON M6G 1M2 Office phone:- 416-537-4800 Cell Phone:- 416-574-4900

96 Simington Ave. Toronto

ቶሮንቶ ቫራይቲ ስቶር

828C Bloor Ste. W.

Fax:- 416-538-2297

E-mail:- berhanet53@yahoo.ca

- Citizenship Application - Appeals - Refugee cases - Detention Reviews - Sponserships - Live in care giver - Pre Removal and Humaniterian Cases

Commissioner of Oath

Tel:-416-743-5111

DHAKA AUTO SERVICES & USED CAR SALE መኪናዎች እንሸጣለን፣ እንዲሁም እንጠግናለን።

We do Mechnical & Body work, Quick oil change, Tming, Belt, Water pump, Transmission, Brakes, any kind of parts and services & for your entire Auto needs.

416-832-1816 * 416-891-1500 1 Musgrave Street, Unit 12 M4E 2H3 Victoria Park & Gerrard

ለመጀመሪያ ጊዜ በሲሚንግተንና በብሉር አካባቢ የቶሮንቶ ቫራይቲ ስቶር ተከፍቶላችኋልና ኑና ጎብኙን! ስልክ ደውሉልን! የምትፈልጉትን ትገበያላችሁ፤ ጠቅለል ባለ ሁኔታ የሚከተሉት ለምስሌ ይኖረል። 1. ፍረሽ አትክልትና ፍራፍሬ ይህ ልዩ ያደርገናል። 2. ቅመማ ቅመም፣ እንጀራ፣ 3. ልዩ ልዩ የግሮሰሪ ሸቀጦች፣ ኮሊንግ ካርድ፣ 4. ሌላም ሌላም...

We sell all sorts of variety items, spices, phone card, Video, C.D. D.V.D. Fruit, Flower and more... Tel:-

416-516-7485

MACELLERIA SAN GABRIELE ቅዱስ ገብርኤል ሥጋ ቤት 416-654-5440 በሳምንት ቀንእሁድ ክፍትክፍት ስንሆን 7 ቀን ከሰኝ5እስክ ነን። እሁድና ሰኞ ዝግ ነን።

ለቁርጥ፣ ለክትፎ፣ ለጥብስ፣ ለወጥ ለመሳሰሉት ትኩስና ንፁሕ ሥጋ በፈለጋችሁት መጠን አናቀርባለን። ለሠርግ፣ ለልደት፣ ለማንኛውም ዝክርና ድግስ ሙሉ በግና በሬ ቢያዙንም በርዎ ድረስ አንኳኩተን እናስረክብዎታለን። 998 St. Clair Ave, W. Toronto (Oakwood & St. Clair)

WORLDWIDE TRAVEL When planning your tripc call us first @

416-535-8872

851 Bloor Street West, Toronto, ON

በኛ በኩል ስትሄዱ ፀሐይ ለፀሐይ ነው መንገዱ።

Reg. # 464--2328


TZTA: Page 2: October 23, 2012 www.tzta.ca

For more information

1678 Bloor Street West, Toronto, ON M6p 1A9

Yohannes Alemayehu Yayeh Sales Representative

ዮሐንስ ያየህ

• Why you rent when you can own one of the beautiful house! • I can arrange a mortgage a lawyer & home inspector for you. • Guaranteed sale of your home. • Real estate information free.

በGTA ቶሮንቶና አካባቢው ቤት መግዛት ወይም መሸጥ ከፍለጉ እንረዳዎታለን።

* ቤት ከመግዝት ወይም ከመሸጥዎ በፊት አስፈላጊ ምክር እንሰጣለን። * ቤት ለመግዛት ከባንክ እንዴት ብድር እንደሚያገኙ ምክርና እርዳታ እንሰጣለን። * የቤት ክራይ ከፍለው ከሚኖሩ በዚያ ዋጋ ተመጣጣኝና የሚስማማዎትን ቤት ለመግዛት እንፈልግለዎታለን። * ቤትዎን ለሽያጭ ስናቀርብ የተለያየ ዘዴ በመጠቀም በጥሩ ዋጋ በአጭር ጊዜ እንዲሸጥ ጥረት እናደርጋለን። * ለቤት ግዢና ሽያጭ ለሚረዱ ጠበቃዎች እንጠቁማለን። * ብቁና በሙያው የሰለጠኑትን እንስፔክተሮች እንጠቁማለን። በተረፈ የቤት መግዛት ወይም መሸጥ ፍላጎተዎንና ጥቅምዎትን ለማርካት በጥሩ ትህትና ባለው መስተንግዶ ከፍተኛ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ ነን። ከዚህ በታች በተጠቀሰው ስልክ ቁጥር Yohannes

416-302-1942

KERA FRESH MEAT ቄራ ሥጋ ቤት

አድራሻችን፡ 2749 Danforth Avenue (Main Street and Danforth Avenue)

ነፃ የመኪና ማቆሚያ አለን።

ለሠርግ፣ ለክርስትና፣ ለድግሥና ለዝክር ሙሉ በግ ሆነ በሬ ምርጥ የሥጋ ብልቶች እዘዙን የሚፈልጉበት ቦታ እናቀርባለን።

Cell:

(416) 769-1616.......Office (416) 302-1942.......Direct

ለክትፎና ዱለት፣ ለጥብስ፣ ለቁርጥ፣ ለወጥ፣ ለቅቅል ለመሳሰሉት የሚሆን ታላቅና ታናሽ፣ ሽንጥና ካለ አይሰጥ፣ ንቅልና ወርጅ፣ ጎድን ከዳቢት ግማሽ ወይም ሙሉ ፍየልና በግ የስጋ ብልቶች ዝግጁ ሆኖ በጥራት በንጽሕና ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል። እናንተ ብቻ ስልክ ደውሉልን መጥታችሁም ጎብኙን።

416-887-6734 * Tel: 416-699-5372

ዮሐንስ ያየህ ብለው ይደውሉ።


TZTA: Page 3: October 23, 2012 www.tzta.ca

ዞብል ሬስቶራንት * ZOBEL RESTAURANT ምሽታችሁን ከድምጻዊ ቶማስ ቴዎድሮስ፣ ከድምፃዊት መሠረት አዲስና ከኪቦርድስት ገዛኸኝ ማሞ ጋር በዞብል ሬስቶራንት እንዲሆን እንጋብዛለን። በሬስቶራንታችን እንደወትሮው ጥራትና ልዩ ጣዕም ያለው ምግብ በማዘጋጀት ከልዩ መስተንግዶ ጋር ተዘጋጅተን እንጠብቃለን።

Tel.:

416-551- 2072

1600 Danforth Ave., Toronto

ምርጥ የጉራጌ ክትፎ በቆጮና በኮባ ካሉ አል መንዲን ይጎብኙ። At Al Mandi, we strive to do things differently by providing an East African and Middle East Dishes. Come and try it! We do Catering for all your special occations Fast Services & Reasonable Price

ለሠርግ፣ለሻዎር፣ ለኒካ ለመሳሰሉት አዳራሽ እናከራያለን

Tel.:- 416-465-4224 www.almandirestaranttoronto.com info@almandirestauranttoronto.com Follow us at www.facebook.com/al-mandi7

24 ሰዓት አገልግሎት የሚሰጥ በዓይነቱና በይዘቱ ብቸኛው የሃበሻ ካፌና ቅመማ ቅመም ሰባተኛ ዓመቱን ምክንያት በማድረግ በተለያዩ እቃዎች ላይ ቅናሽ አድርጎ ሊያስተናግዳችሁ ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል። እንጀራ፣ በርበሬ፣ የተለያዩ ቅመማ ቅመሞች፣ የኢትዮጵያ እንጀራ፣ ቆጮ፣ የተለያዩ የግሮሰሪ ዕቃዎች ሌላም ሌላም አሉን ብቅ ብላችሁ ጎብኙን።

416-363-4746 Cell:- 416-801-1974 Tel.:-


TZTA: Page 4: October 23, 2012: www.tzta.ca

MAX FINANCIAL SERVICES Loan & Line of Credit Consultant

You need money!

1. Loan 2. Line of Credit 3. Credit Card 4. Secured Line of 10 - 50k from the Banks Credit For further information call Joseph Haile @

416-854-8593

no Problm Trust me

100 Cowdray Court Suite 330 Scarborough, ON M1S 5C8 joseph.mfs@gmail.com


TZTA: Page 5: October 23, 2012: www.tzta.ca

አዲሱ የቅድስት ማርያም ካቴድራል በቶርንቶ ሊመረቅ ነው

ሊቀ ካህናት ምሳሌ እንግዳ ይህ አዲሱ ቤተ ክርስቲያን በሚመጣው ኖቬምበር 17 ቀንና ኖቨምበር 18 ቀን በታላቅ ክብር ሊመርቅ በመሆኑ የትዝታ ጋዜጣ አዘጋጅ ይህን ምክንያት በማደረግ ከዋናው አስተዳዳሪ ከሊቀ ካህናት ምሳሌ ጋር ያደረገውን ቃለ መጠይቅ በሚቀጥለው ሁኔታ ቀርቧል።

ሊቀ ካህናት ምሳሌ ይህን ቃለመጠየቅ ለማድረግ ስለፈቃዱልኝ በጣም አመሰግናለሁ። ሊቀ ካ ህ ና ት ፦ በተደጋጋሚ ስለቤተክርስትያናችን የሚደረገውን ሁኔታ መጥተው በመጠየቅዎ በጣም አመሰግናለሁ።

ትዝታ፦ ይኽው በእርሶና በህዝቡ ጥረት እንዲሁም ከእግዚአብሄር እርዳታ ጋር ቤተክርስቲያናችን ተሰርቶ አልቆ ሊመርቅ ነው፣ ስለዚህ ምን ሀሳብ አለዎ? ሊቀ ካ ህ ና ት ፦ እንግዲህ በቃላት ተነግሮ የሚፈጸም አይደለም፣ እንዲሁ ባጭሩ ሃያሉ እግዚአብሔር በኛ አድሮ የማይቻለውን

እንድንፈጽም እንድናከናውን ፈቅዶአል። በመሰረቱ በዚህ በቶሮንቶ ያለነው ምእመናን በጉልበትም በገንዘብም በጥበብም ቢሆን አዲስ መጭዎች እንደመሆናችን መጠን ይሄን ያህል በሚሊየን የሚያወጣ ህንጻ ለመስራት አቅማችን አልነበረም፣ ነገርግን የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል እኛም ባሮቹ ተንስተን እንሰራለን ብለን ጀመርን። እንግዲህ ይህ በመጽሐፈ ነብያት ተጽፎ ተመዝግቦ ያለ ነው፣ ያለፉት አባቶቻችን አምላካቸውን ተማምነው የሰሩትን ስራ በማውሳት ጀመርነው እግዚአብሔር ግን አከናወነ ስለዚህ የምንለው አንደኛ ለዚህ መነሻ የሆነውን አምላካችንን እናመሰግናለን ሁለተኛ ደግሞ በዚህ በቶሮንቶና አካባቢው ያለው ምእመናን ለዚህ ድንቅ ስራ መሳሪያ ሆኖ መዘጋጀቱን በጣም አመሰግናለሁ። ትዝታ፦ ተከታዩን ገጽ 4 ይመልከቱ

Don Mills Career College For Health, Business and Technology Registered as a private career college (PCC) under the Private Career College Act, 2005

EARN DIPLOMA AT DMCC WITHIN 4 TO 11 MONTHS * Office Administrator * Computer Application Office Administrator * Accounting Payroll Administrator * Early Childhood Assistant

You may qualify for second career

EI, Welfare, WSIB, OSSP recipients and New Immigrants Welcome

For more information Call:

647 348 3622

የምንሰጣቸው አገልግሎት

10 Gateway Blvd. Unit # R 160, Toronto, ON M3C 3A1 Email: info@donmillscollege.com * Website: www.donmillscollege.com

GREAT Trained Driver for Tomorrow

TRUCK & FORKLIFT DRIVING SCHOOL 100% owned & Operated By Canadians

TRAINING * LICENCE *JOB Truck

AZ $599.00

Bus

BCDEF $299.00

FORKLIFT $98.00

Our Qualified instructor Ensure The Quality Trainng CLASSES A,B.C,D,E,F,G,z & Forklift.

Tel:- 416-745-5700 2552 Finch Ave. W., Unit # 103 Website: www.great truckschool.cm

_- የሴቶች የወር አበባ ችግር - አለርጅክን በተመለከተ - እንቅልፍን ማጣት - ክብደት ለመቀነስ - የቆዳ በሽታ በተመለከተ - ቁርጥማትና ድንዛአዜ - ራስ ምታትን በተመለከተ - የወንድ ልጅ ችግር ካለ - መሃንነትን በተመለከተ - ፍርሃትን መፈወስ - መደበርን መፈወስ - ልብ በሽታና ስትሮክ - አልክሆል፣ ሲጋራ ሱስ - የፀጉር መመንመን ጉዳይ

ለመሳሰሉት ሕክምና ለመስጠት ሙሉ ሕጋዊ ፈቃድና ዋስትና አለን።


TZTA: Page 6: October, 2012: www.tzta.ca ከገጽ 5 የዞር እርሶ ለዚህ ምን ይሰማዎታል?

ሊቀካህናት፦ እንግዲህ ስለእኔ በመጀመሪያ ደረጃ የተሰማኝ ስሜት ቶሮንቶ እንደመጣሁ ከአንድ አመት ተኩል በኋላ ነው ሙሉ በሙሉ የእግዚአብሔርን ጥሪ ለመቀበል የወሰንኩት፣ ስመጣ ቄስ ሁኜ ነው፣ የመጣሁት ከዚያ በፊትም በቅስና ሳገለግል ነበር፣ ይሆነ ሁኖ ግማሽ ሃሳብ ነበረኝ ተምሬ ለዚህ አለም ኑሮ የሚያመቻችና የሚበቃ እውቀት ኖሮኝ ወደ አገሬ ተመልሼ ለመስራትና የዚህን አለም ህይወት በሰፊው ለመያያዝ ነበር ምኞቴ፤ አንድ አመት ተኩል ከቆየሁ በኋላ ግን እግዚአብሔር ያዘጋጀኝ ለዚህ ሳይሆን ለመንፈሳዊ አገልግሎት እንደጠራኝ ተገንዘብኩ። ድሮም መጀመሪያም ሳጠናው የነበረውን የቢዝነስ ጥናት አቋርጬ ቲዎሎጂ ገባሁ። ቲዎሎጂው እንሊዘኛው ሰከንድ ላንጉዊጅ በመሆኑ በጣም ቢያስቸግርም ሆኖም ብጽናት ስለያዝኩት በጥሩ ሁኔታ ማስተር ኦፍ ዲግሪዬን ከያዝኩ በኋላ አድቫይዘሬ ወደ ፒ.ኤ.ች ድግሪ እንድሄድ ሙሉ እስኮላር ሽፕ እንደሚሰጠኝና ነገርግን ከዚህ ወጥቼ ካልጋሪ እንድሄድ ምክር ሰቶኝ ነበረ። ኮርሱ እዳለቀ የዩኒቨርሲቲው አስተማሪ ትሆናለህ፣ ደሞዝም በርከት ያለ ታገኛለህ የሚል ነበረ የነገረኝ፣ ግን መጀመሪያ ወደ ቲዎሎጂው ስገባ የሱን ጥሪ ተቀብዬ ወደመንፈሳዊ አገልግሎት ትቼ መሄድ ሁለተኛ ከፍተኛ ደሞዝ አገኛለሁ ብዬ ሌላ ቦታ መሄድ በምንም አይነት ለኔ የሚጠቅም እንዳይደለ ወሰንኩ፣ ከዚያ በኋላ ስራ ጀመርኩ። በአካባቢዬ ያሉ የቶሮንቶ ንዋሪ የሆኑ ምእመናን እጅግ የተቀደሱ በመሆናቸው በጣም እደሰታለሁ። ሁልግዜ በሰበካ ጉባዔው አብረውኝ የሚሰሩ ከመጀመሪያው ጀምሮ እስካሁን ድረስ የተለያየ ሰበካ ጉባዔ እየተመረጠ አብረን እንሰራለን፣ አንድ ቀንም ያለመግባባት ተፈጥሮ አያውቅም፣ ሁል ጊዜም በስምምነት በመተባበር እንስራ ነበር፣ ለዚህ በጣም እደሰታለሁ፣ ያ ሁሉ በጣም ያስደስተኛል። መጀመሪያ ህንጻውን ስንጀምረው አፋችን እንዳመጣ ከአራት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ድረስ የሚፈጅ ነው ብለን ነበር ያሰብነው፣ ይህውም በግርድፉ ከመሃንዲሱ የተስጠንን ሃሳብ በመያዝ ነው፣ እና እሱ ሲጀምር በኢትዮጵያ ባህል መሰረት እንዲሰራ ስንጠይቀው አንድ የተናገረኝ ነገር ነበር፣ ሰውዬው ጣሊያናዊ ነው፣ መሃንዲሱ የኢትዮጵያውያን ጥንታውያን ቤተክርስትያን በፎቶ የተደገፈ ሳቀርብለት፣ እንደዚህ ነው መሰራት ያለበት ብዬ ስለው፣ ይህ እኮ በጣም ውድ ነው! ለመሆኑ ለስንት ጊዜ የሚቆይ ቤተክርስትያን ነው የምትፈልገው? አለኝ። አንተ ጣሊያናዊ አይደለህም እንዴ? አልኩት። አዎ! ጣሊያናዊ ነኝ፣ የባቲካን ሮም ያለው ቤተክርስቲያን ስንት አመት ነው የቆየው? ምን ማለት ነው? እኮ ስንት ዓመት ነው? ንገረኝ! አልኩት። እኛ የምንፈልገው ለዘለዓለም እንዲቆይ ነው፣ እንደቫቲካን እኮ ብዙ ያስፈልጋችኋል ማለቴ ነው። ምንም እንክዋን እንደቫቲካን ቅዱስ ጴጥሮስ ቤተክርስትያን ያማረ ባይሆንም መነሻው እንደዚያ ነው ብዬ ስነግረው፣ እርግጥኛ ይሄን ቤተክርስትያን ዲዛይን ሲያወጣ ከላሊበላ፣ ከአክሱም፣ ከቅዱስ ስላሴ እየወሰደ ጨማምሮ ነው፣ እንደዚያ ነው ያወጣው፣ በዚህ በጣም እደሰታለሁ። በመጀመሪያ ዲዝያኑን ሲያቀርብልኝ በጣም ነው የተደሰትኩት፣ አሁን ግን የበለጠ እንዳየኽው፣ በኛ በሰው እጅ የተሰራ አይደለም፣ እግዚአብሔር እንዴት ይወደናል። ዮሴፍ የተባለው ሰው ውንድሞቹ ለሃያ ብር ሽጠውት ግብጽ በሄደ ግዜ የሱን መሸጠና መሰደድ እግዚአብሄር ስለባረከው ለትውልዱ ቤዛ ሆኖላቸዋል። እሱም ወንድሞቹ እደገና ሲሄዱ አይዞአችሁ አትደንግጡ ይህንን ቅሬት እንዳይዝባችሁ እግዚአብሔር አስቀድሞ ፕላን አውቶ ስለነበር ነው። ምናልባትም አሁን ቁጭ ብዬ ስገነዘበው ወደ ላይ በዶሙ ወስጥ የክርስቶስን ምጻት የሚያሳየውን ስእል ሳይ “እግዚአብሔር አምላክ ሆይ እኛን ወደዚህ ያመጣኽን ለስደት ሳይሆን ያንተን ድንቅ ስራ እንድናይነው የመረጥከን” እያልኩ እራሴ በየቀኑ ነው የማመሰግነ፣ የኔ ምስጋና በቂ አየደለም ብዬ ብገምትም በየቀኑ ነው የማመሰግነው እጅግ እጅግ በጣም ደስ እያለኝ ነው። ይሄ ቤተክርስትያን ያስደሰተኝ ሕንጻው ብቻ ጥሩ በመሆኑ አይደለም። ይሄ ሕዝብ፣ “የኢትዮጵያ ሕዝብ ምን አይነት ድንቅ ሕዝብ መሆኑንም አስተምሮኛል” አብዛኛውን እንደሚታወቀው በዚህ በቶሮንቶ ያለ ምእመናን በመጠነኛ ገቢ የሚኖር ነው። በክሬዲት ካርድ ነው እየከፈለ ያሰራው፣ እስካሁን ድረስ ለተሰራው ስራ ስድስት ነጥብ አንድ! ደርሶአል ስድስት ነጠብ አንድ ሚሊየን ማውጣት ለዚህ ህዝብ ታምር እንደተፈጠረ ነው የማየው እና “ለካ ህዝብ አለ ለካ እግዚአብሔርም በስደትም እኛን አረሳንም፣ እኛ ፈቃደኛ ሆነን እንተባበር ካልን እንደሚያስተባብረን አየሁ በብዙ ነገር ስመለከት እግዚአብሔር እሱ እኛ ፈቃደኛ እስከ ሆንን ድረስ እኛን አንድ ማደረግ ይችላል” ብዬ ደምድሜ አለሁ። ትዝታ፦ ይህ የቤተክርስትያን ህንፃ በሚስራበት ሰአት ከጎኖዎት ሳይለዩ ደከመን ሰለቸን ሳይሉ ጊዜአቸውን ለዚህ ቅዱስ ስራ አሳልፈው ለስጡት ምእመናን የሚያስትገላልፉት መልክት ካለ? ሊቀካህናት፦ ለእዚህ መልስ መቸም ቃላት ያንሰኛል፣ ቀደም ብዬም ተናግሬዋለሁ። ስንጀምር ብዙ ገንዘብ አልነበረንም፣ የጀመርነው የተወሰነ ገንዘብ የዘን ነው። አንዳንድ ሰዎች የኢኮኖሚ እውቀት ያላቸው በስራም አመክሮ ያላቸው፣ ቢያንስ አንድ ሚሊየን ሳትይዙ እንዴት ታስቆፍራላችሁ ብለው ነግረውኝ ነበር፣ ነገር ግን ቅድም እንደተናገርኩት የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፣ እኛ ባሪያዎቹ ተነስተን እንሰራለን፣ ይሄ ነበረ መልሴ። እንግዲህ በዚህ አጋጣሚ በጠቅላላው የቶሮንቶ ህዝብ ማለት ይቻላል ከዚያም አልፎ ከቶሮንቶ ውጭ ያሉ ብዙ የረዱን አሉ፤ አንደኛ በገንዘባቸው፣ በእውቀታቸው፣ በጊዜአቸው መስዋዕት የሚያደርጉት አብዛኛዎቹ በተለይ ሁለተኛውን የህንጻ ስራ ማለት ፌዝ ዋንን ጨርሶ ፌዝ ቱ ሲጀመር ወይም ደግሞ ሁለተኛው ክፍል ሲጀመር የተሰራው በፈቃደኞች ወይም በቮለንቴር ነበር። ነገር ግን ይህንን ስንጀምር መሃንዲሱ ኮንስትራክሽን ማናጀር ያስፈልጋል፣ እንደዚያ ካልሆነ አልሰራም ብሎ ነበር። ስናጠያይቅ ለዚህ ስራ ቢያንስ አንድ መቶ ስልሳ ሺህ ዶላር በአመት የሚከፈለው

መሆን አለበት ነው የተባለው። እከሌ እከሌ ብዬ ስም አልጠራም ብዙ አዋቂዎች፣ ብዙ እንጂኔሮች በዚህ ሕንጻ ስራ ተካፍለዋል። ለምሳሌ በወቅቱ አንደኛው እንደማናጀር ሆኖ መሥራት ይችላል፣ ነገር ግን እውቀቱ ቢኖረውም ላይሰንስ አልነበረውም ስለዚህ መሥራት አልቻለም። ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ፣ ብዙ ላይሰንስ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ተገኙ። የማሃንዲሱን ቋንቋ የሚያውቁ እኛ አለን እኛ ከመሃንዲሱ ጋር በመሆን እንሰራለን በማለት ፈቃደኛ ስለሆኑ መሃዲሱም ተቀበለን። መሃንዲሱ እንደገመተው ከአራት እስከ አምስት መቶ ሺህ ድረስ ይሆናል ያለው ገንዘብ በነዚህ በጎ ስራተኞች ምክንያት ዳነ። የቶሮንቶ ምእመናን ወንዱም ሴቱም እግዚአብሔር ትውልዱን ይባርክ። የተወለዱትን ሕጻናቶች እግዚአብሔር ያሳድግ፤ በተለይም በእውነቱ እግዚአብሔርን የምለምነው ለዚህ ሕዝብ ነገ ተነገ ወዲያ ቢቸገር ምጥቶ ችግሩን ለፈጣሪው ነግሮ ከችግሩ የሚድንበትን፣ ቢታመም ለፈጣሪው ነግሮ የሚፈወስበትን፣ በሃጢያት ቢወድቅ እንክዋን በዚህ ቦታ የሚቀርበው መሰዋእትና ቅዳሴ ከሃጢያት ነጻ እንዲያደርጋቸው ወደፈጣሪያቸው እንዲመለሱ እምመኘው ይህንን ነው። ይሄ ትውልድ የተባረከ ትውልድ ነው፣ ቃላት ያንሰኛል ብዬ የተናገርኩትም ለዚህ ነው፣ በጣም እጅግ የሚያኮራ ህዝብ ነው፣ በዚህ አጋጣሚ ሌላ የምናገረው “እኛ እግዚአብሔርን አምነን የምንነሳ ከሆነ ተባብረን መብላት ብቻ ሳይሆን፣ ሰዎች የሚመሰክሩት በኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር አሁን አብሮ መብላት ይችላል፣ አብሮ መስራት ግን አይችልም እያሉ ነውና እኛ ግን አስመስክረናል። የቶሮንቶ ሕዝብ አብሮ መስራትም ይችላል ይሄው አብረን ሰርተናል እና እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። የቶሮንቶን ሕዝብ በመላ የመንበረ ብርሃን ካቴድራል ቅድስት ማሪያም አክቲቭ የሆኑ አብላቶች የዚህ ቤተክርስትያን ተመዝግበው አባል የሆኑትን ብቻ ሳይሆን በጠቅላላ በቶሮንቶ የሚኖረው ኢትዮጵያውያን የተባረከ ምእመናን መሆኑን ነው ያየሁት እግዚአብሔር ትውልዱን ይባርክ እላለሁ።

AFKEA Business Consultant & Accounting

• Small Business Consultant • Income Tax – Personal & Business • Money Transfer (Tawakal Express) to Eritrea, Ethiopia and others Other Applications

16 – 262 Parliament st. (south of Dundas) Toronto M5A3A4) Call Almirah Afkieh

416-268-9070 aafkieh@yahoo.com

Colosseo Painting & Decore

The Power of Co “Colour suitsour personality and our spaces has the power to make us happy”.

Dawit Abu Interior Designer

ት ዝታ፦ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ለመስጠት፣ ከቫን ሮድ አንስቶ ብሉር ስትሪት ከዚያም በሰማንያ ታይኮስ ዌር ሃውስ ተገዝቶ በተከታታይ ትዝታ ስትዘግብ ቆይታለች ለንባብም አብቅታለች። እስኪ አሁን ያለው አዲሱ ህንጻ ቤተክርስቲያን ከአጀማመሩና እስካሁን እስከምርቃት መዳረሻው ድረስ ያለውን ሁኔታ ለግንዛቤ ያህል በገልጹልን? ሊቀካህናት፦ እንግዲህ ከዛሬ አስራ አምስት አመት በፊት ከኪራይ ቤት ተነስተን አሁን ያለንበትን ሰማኒያ ታይኮስ ዌር ሃውስ ገዝተን ስንጀምር የዚያም ጊዜም ገንዘብ አልነበረንም። ይህንን ገዛን ብለን ስንጨርስ ሁለተኛው ኩታ ገጠም የሆነው ስማኒያ አራት ታይኮስ በሃራጅ ለሽያጭ ቀረበ። ይህንንም መግዛት አለብን ስል ብዙ ሰዎች የተሳለቁም አሉ! የተናደዱም አሉ! በአንጻሩ ደግሞ እውነት ነው እዚህ ላይ ሌሎች የዳንስ ምሽት የሚያደርጉ ቢገዙት ምን እንሆናለን ስንል፣ ልክነው ብለው ተገነዘቡ፣ በዚህ የተነሳ ሁለቱንም ህንጻ ገዛን። ስንገዛ ገንዘብ አልነበረንም። በዚህ አጋጣሚ ታሪካቸውም እንዲወጣ ስለምፈልግ አቶ ስዩም ካሳ የተባሉ ወንድማችን የዚያን ጊዜ የህንጻ ኮሚቴ አባል ሆነው ይቀሳቀሱ ነበርና ባንክ አላበድርም ስላለ በአቶ ስዩም ካሳና በክቡር አንባሳደር ግርማ፣ በአቶ ፋሲካ ምትኩ አማካይነት ቤታቸውን ለባንክ እናሲዛለን ብለው ፈርመው በመቅረባቸው ነው ልናገኝ የቻልነው። እንግዲህ ይሄ የሰማኒያ ታይኮስ አምስት መቶ ሺህ ሲሆን የሰማኒያ አራት ድግሞ ሶስት መቶ ሺህ አምስት መቶ ነበር። በድምሩ ስምት መቶ ሺህ ነው የተገዛው። ይህንን ስንገዛ በኪሳችን ስላልነበረን በነሱ አማካኝነት ነው የተገዛው በተለይም እዚህ ላይ ደግሜ እናገራለሁ አቶ ስዩም ካሳ በቢዝነስ በብዙ ይሯሯጥ ስለነበረ ይሄን ነገር የፈጻሙልን አቶ ስዩም ካሳ ነበሩ። አሁንም እግዚአብሔር እሱንም ቤተሰቡንም ይባርከው። ከዚያ ከአምስት አመት በኋላ ነው ባንኩ እንቅስቃሴአችንን አይቶ ብድር የሰጠንና እነሱን ከዚያ ነጻ ያወጣናቸው። ይሄ በዚህ እንዳለ፤ መጀመሪያውኑ ይህንን ስንገዛ በራሴ እምነት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን በኢትዮጵያ ባህል የታቀፈ ቤተክርስትያን ማሰራት አለብን የሚል እቅድ ነበረኝ፣ ነብሳቸውን ይማርና አቡነ ይሳቅ እሳቸው ናቸው ውደዚህ አገር እንድመጣ ያደርጉኝ፤ እዚህ በመጡ ጊዜ ሲጠይቁኝ፣ መቸ ነው ከዚህ ዌር ሃውስ የምትወጣው? ሲሉኝ ብፁእ አባታችን የአስር አመት ጊዜነው የሚወስድብን ይመስለኛል አልዃቸው። በእርግጥ ከአስራ ዓመት አልፎአል። አባታችንም ያሉት ጥሩ ነው! አዎ! በአስር አመት ውስጥ እንደምታሰራ አውቃለሁ። እሳቸው በህይወት የሉም። ባጸደ ንብስ ሆነው ይመለከቱታል። የዛን ግዜ እንደገባን ነበር የታቀደው። ትዝታ፦ እንዴት ታቀደ? ሊቀካህናት፦ ያ በግለሰቦች የተገዛውን ንብረት ወደ እኛ አዙረን ባንኩ ሲያበድረን፣ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ፈንድ ሬዚንግ ገንዘብ ማሰባሰብ ጀምረን። ግን የህልም እሩጫ ሆነ። እንዲሁ ሲባል፣ እንዲሁ ሲባል፣ እንዲሁ ሲባል፣ ምንም ከፍ አላለም። ገቢው ለማጠናከር የድሪሙ ሃሳቡ ግን ህዝቡ ላይ እየጎላ ነው የሄደው። በአንጻሩ ደግሞ ሌላ ተቃዋሚ ነበር። እነዚህ ሰዎች ሁሌ ቤተክርስትያን ይላሉ ነገር ግን ሰርተው አያሳዩም የሚባል ይወራ ነበር፣ እንዲያውም ተስፋ የሚያስቆርጥ ነበር። እኔ እንኳን ተስፋ ቆርጬ አላውቅም፣ ሌሎች ሰዎች ግን በጣም ተስፋ ቆርጠው ነበር። እኛ በነጻ እያገለገልን ደግሞ እንዲህ አይነት አባባል የሚል ስሜት ይሰማ ነበረ። ግዴላችሁም የሚሰራ ሰው ሁልጊዜ ስሙ ይነሳል፣ ስራችሁን ቀጥሉ እያልኩኝ፣ እኔንም እንዲሁ ሲሉኝ፣ እኔ ለነገሩ ደንቆኝም አያውቅም! ተደንቄም አላውቅም! አዝኜም አላውቅም! ተቆጥቼም አላውቅም! አኩርፌም አላውቅም! በኔ ላይ ብዙ ወቀሳ ቢመጣ፣ አንዴ እንዲያውም ባለቤቴን ሁል ጊዜ የምላት ይሄ ህዝብ ሌላ ሰው የለውም፣ ስሜቱን ንዴቱን የሚወጣበት የኔ ስም ከሆነ ምናለበት፣ ምን አናደደሽ! ቀጣዩን ገጽ 12 ይመልከቱ

DUFFERIN CUSTOM UPHOLSTREY & DECORATION 2350 DUFFERIN STREET TORONTO, ON

We do new custom made:- Sofa, Chair, Headboard, Slip Cover & Window Seats. For your old furniture we do:- Re upholstery, Restyle, Restoration & Replace foam cushion. ማንኛውንም ዓይነት በጨርቅም ሆነ በቆዳ የሚሠራ የእንግዳ መቀበያ፣ የምግብ ቤት፣ የመኝታ ቤት፣ መጋረጃ እቃዎችን በውቅ እንሠራለን። እንዲሁም ያለዎትን ጥገና የሚያስፈልጋቸው እቃዎች በጥሩ ሁኔታ የማደስ ችሎታ አለን። * ያለዎት ሶፋ (sofa)እስፕሪንጉ እረግቦ እንደሆነ * ያለዎን ቅርፅና መጠኑን መቀየር ከፈለጉ * እስፖንጁን መቀየር ያስፈልገው እንደሆነየእግሩን ቅርጽና ቀለም መቀየር ከፈለጉ

አቶ ሃይሌ ማኔጀር

በስልክ ቁጥር

416-546-1501

በመደወል ሐይሌን ያነጋግሩ።

Melaku Asamenaw

Financial Services Manager

Bank of Montereal

For Bank Need

* Morgtgage * Loan * Investment Mutual Fund *Personal Line of Credit & Master Card * Everyday Bank Ac-

count * etc...

Tel:

416-867-2830 * Fax: 416-867-7769 BMO Bank of Montereal

2 Queen Street East, Toronto, ON M5C 3G7 melaku.asamenaw@bmo.com

ለንግድ የሚሆን ቤት እንሸጣልን

ሚር ጆርዳን ሃድገት በ1600 Danfprth Avenue, Toronto የሚገኘውን የንግድ ቤት መሸጥ እንፈልጋለን። ቤቱ አሁን ዞብል ሬስቶራንት የሚገኝበት ሲሆን አብዛኛውን ለኢትዮጵያውያን ቢዝነስ በሚገኝበት አካባቢ ነው። ይህን በግል ለመሸጥ ስለምንፈልግ ፈላጊዎች በሚቀጥለው ስልክ ማድርግ ወይም ኢ-ሜል ማድረግ ይቻላል።የመጨረሻው ቀን ኦኮበር 31 2012 ይሆናል። HOME TO HOME REALTY INC., BROKERAGE 1109 - 60 Ruddington Drive, Toronto M2k2J9 OLGA KUDRYAVTEVA, Broker

Tel:- 416-454-9757 Fax: 647-346-7312


የስፖርት አምድ

TZTA: Page 7 : October 23, 18, 2012 www.tzta.

ባለፈው መስከረም የኢትዮጵያ ቀን የቅድስት ማርያም ስፖርት ክለብና ሀሚልተን የሚገኘው የወጣቶች ስፖርት ቡድን በክርስቲ የእግር ኳስ ግጥሚያ አደርጉ

የቅድስት ማርያም ስፖርት ክለብ

በቶሮንቶና አካባቢው የሚገኘው የኢትዮጵያ ማኅበር በክርሰቲ ፓርከ ላይ ለ5ኛ ጊዜ የኢትዮጵያውያንን አዲስ ዓመት ሞቅ ደመቅ ባለ ሁኔታ የተፈጥሮ ዝናብ ሳይበግረው እንደወትሮው ጭዋነትና ሥርዓት በተሞላው ሁኔታ አክብሮ ውሏል። በዚህም ታላቅ ክብረ በዓል ላይ በርካታ ታዳሚዎች ሲገኙ በመዲናችን የሚገኙ ታላላቅ የሃይማኖት መሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዳዎች እንዲሁም ከከተማችን ወጣ በሎ ከምትገኘውም ሀሚልተን ከተማ በርካታ ኢትዮጵያውያን የእግር ኳስ ተጫዋቾቻቸውን በመያዝ ቀደም ብለው ተገኝተዋል። ለዚህም በዓል ላይ ከፍተኛ ድምቀት ከሰጠው አንዱ ወጣት ኢትዮጵያውያን አልባሌ ቦታ እንይውሉና ጤነኛ ሁነው እንዲያድጉ እንዲሁም የነገውን ኮሚኒቲ ተረካቢ እንዲሆኑ እንዚህን ወጣቾች በማሰባሰብ የበጋውን ወራት በሙሉ አገልግሎት የሚሰጡትን ወገኖችና ወላጆች ጭምር ለልጆቻቸው ሕይወት መዳን ለሚከፍሉት መሥዋዕትነት በርቱ ተበራቱ በማለት ልናመሰግናቸው ይገባል። በዚህ የዝግጅት ዕለት የእግር ኳስ ግጥሚያ ያደረጉት በቶሮንቶ ከተቋቋመ 3ኛ ዓመቱን የያዘው የቅድስት ማርያም ስፖርት ክለብና ሀሚልተን የሚገኘው የወጣቶች ስፖርት ቡድን ነበር። ከአንድ ሳምንት ቀደም ብሎ ማለትም ነሐሴ 26 ቀን 2004(Sep 1st ,2012) ዓ. ም. ሀሚልተን የሚገኙት ኢትዮጵያውያን የአዲሱን ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ በወ/ሮ ገነት አሰተባባሪነት የስፖርትና የሙዚቃ ዝግጅት እንዲሁም የምሳ ግብዣ አድርገው ነበር። ቡድኑና ደጋፊዎቹ በቦታው ሲደርሱ እንኳን ደኅና መጣችሁ በማለት ተቀብለውታል ። በመቀጥልም የታዳጊ ወጣቶች ማለትም ከ14 ዓመት በታች የሆናቸው ተጋጥመው የሀሚልተን ቡድን ሲያሸንፍ ከዚያ በላይ ዕድሜ ያላቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑት ደግሞ ተጋጥመው የቶሮንቶ ቅድስት ማርያም ቡድን አሸንፎ ሁለቱም ቡድኖች የተዘጋጀላቸውን የዋንጫ ሽልማት ከዕለቱ የክብር እንግዳ በሀሚልተን የኢትዮጵያ ማኅበር ሊቀመንበር ከአቶ ተሾመ ተቀብለዋል። በዚህ አጋጣሚ አሰልጣኝ

ሀሚልተን የሚገኘው የወጣቶች ስፖርት ቡድን

አቶ ካሊድን አስተባባሪ ወ/ሮ ገነትንና መላውን የሀሚልተን ኅብረሰተስብ ላደረገው መስተንግዶ የባርቤኪው፣ የተለያዩ የምግብ ዐይነትና የበቆሎ ጥብስ የሀገር ቡና ግብዣ ከልብ እናመሰግናለን። በመዲናችን በቶሮንቶ ደግሞ ጷጉሜን 3 ቀን 2004(Sep 8.2012) ዓ. ም. በተዘጋጀው የኢትዮጵያ ማኅበር የአዲስ ዓመት በዓል ላይ የእግር ኳስ ግጥሚያ ያደረጉት የቶሮንቶው የቅድስት ማርያም ስፖርት ቡድንና የሀሚልተኑ የእግር ኳስ ቡድን ነበሩ። በዚህም በርካታ ተመልካች በነበረበት ግጥሚያ በታዳጊ ወጣቶች እድሚያቸው ከ14 ዓመት በታች በሆነው ግጥሚያ የቶሮንቶ ቡድን ሲያሸንፍ እድሚያቸው ከ16ዓመት በታች በሆነው ደግሞ የሀሚልተን ብድን አሸንፏል። የሀሚልትን ብድን በአሰልጣኝ ካሊድ ጠንካራ አመራር አዳዲስ ተጫዋቾችን አዘጋጅቶ በመምጣት በሀሚልተን ያጠውን ዋንጫ በቶርንቶ በማግኘቱ በዋንጫ ሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከደጋፊዎች የተሰጠው ድጋፍ አስመስክሯል። ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲህ ተጠናክረው በማየታቸውም ብዙ ሰዎች ተደስተዋል። በዚህም በዓል ላይ በመገኘታቸው አሠልጣኝ ካሊድ፣ የማኅበሩ ሊቀ መንበር አቶ ተሾመና እንዲሁም ደጋፊዎቹ ወ/ሮ ገነት በዚህ ታላቅ በዓል ላይ ጥሪ ያደረገላቸውን የኢትዮጵያ ማኅበር በቶሮንቶና አካባቢው እንዲሁም የቅድስት ማርያንመ ስፖርት ክለብ አሠልጣኝ አቶ ዓለማየሁ አየለ ፣ አቶ ዳሙሽ መለሰን፣ የቡድኑን መሪ አቶ ዓለም ገ/አምላክንና አቶ ዘወንጌል አማኑኤልን አመስግነው ለወደፊት በተያዘው ዕቅድ የኪችነርንና የኦታዋን ወጣቶች በዚህ መልክ ለማገናኘት በሚደረገው ጥረት ዋንኛ ተሳታፊ እንደሚሆኑ ገልፀው ከልብ እያመሰገኑ ለመላው ታዳሚ እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል። በዕለቱም የተዘጋጀላቸውን የዋንጫና የመዳልያ ሸልማት ከዕለቱ የክብር እንግዳ የኢትዮጵያ ማኅበር ሊቀ /መ የዋንጫና የመዳሊያ ሽልማት ተቀብለዋል። ዓለም ገ/ አምላክ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ለአፍሪካ ዋንጫ አለፈ

ደቡብ አፍሪካ ለሚደረገው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከሱዳን አቻው ጋር ዛሬ ጥቅምት 4 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታድየም ጨዋታ ያደረገው የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን 2 ለ 0 በማሸነፉ ከ 31 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳታፊ ለመሆን ቻለች፡፡

አለው ግርማ ሞገስ

አለው ግርማ ሞገስ እንዲሁም ችሎታ ህዝቡን አስደሰቱት በእግር ኳስ ጫወታ አዳነና ሰላዲን የመቷት በቴስታ ለማለፍ አበቃቸው አገር አስጠርታ የኋላ ደጀኑ ከጀማል አንስቶ ስዩምና ደጉ ብርሀኑን አካቶ የብረት አጥር ነው በቢያድግልኝ ተረድቶ ያያችሁ እንደሆን አስራትን በመሀል የሚያልፈውም የለም ሁሉንም ይጥላል ጌታነህ ከበደ አለው ግርማ ሞገስ ፍጹም ያስደስታል ኳሷ ላይ ሲደንስ አዳነ ግርማ የኳሷ ንጉስ ነው ሰላዲን ሰይድ መረቡ የሱ ነው ምንያህል ተሾመ አስራትን ጨምረው ዘጠና ደቂቃ ህዝቡን አስፈንድቀው በሱዳንም ሆነ ባገር ላይ ጫወታ

ኢትዮጵያ ሲጫወት ኳሷን ሲመታታ ለትውልድ የሚሆን የሰጡት ትዝታ ! ለሰላሳ ዓመት ስሟ ሳይጠራ ተረስቶ የቆየ ያገርን ባንድራ በፍቅሯ በታሪክ ቋሚ እንዲኮራ ይድነቃቸው ተሰማ ላገሩ ሲሰራ እነ መንግስቱ ወርቁ ያሳዩት ሲያኮራ የዛሬ ትውልዶች በህብረት በጋራ በስታዲዮማችን ፍሬዋ ጎመራ ይኋው አለች ዛሬ ችቦዋ እንደበራ እኔም ልቤን አለው ደስ ደስ ሊነገር ነውና ስምሟ ሊወዳደስ የወንዶቹ አገር ኢትዮጵያ ልትሞገስ ይገባኛል እና ስማችሁን ላወድስ ጌታነህ ከበደ /// ጌት ቄራ ///

We are your #1 value to the world! Travelair has been serving the African community for over 25 years. Let our experienced agents book your travel arrangements on Ethiopian Airlines, KLM, Lufthansa, Air France, Brussels Airlines, Emirates, and many more! We have EXCLUSIVE rates and seat sales to Abidjan, Abuja, Accra, Addis Ababa, Dar es Salaam, Kigali, Luanda, Libreville, Lagos, Nairobi, Douala, Bamako, Bujumbura, Conakry, Kinshasa, Kampala, Freetown, Monrovia, Dakar, Khartoum, and many more! We are a full service Travel Agency and can book all your Holiday needs, including: All inclusive, Hawaii, Cruise, Disney, Las Vegas, Europe, and even cover your Travel Insurance needs!

we are currently looking for an experienced Travel Agent with their own existing clientele.

Travelair International Inc.

416-964-1950

569 Yonge St. Toronto, ON www.etravelair.com / info@etravelair.com

Reg#50011608


TZTA: Page 8: October 23, 2012 www.tzta.ca

ግጥም ወግድልኝ ወዲያ!

አሥራዯው (ከፈረንሳይ) ሲጭኑህ አጋሰስ፤ ሲጋልቡህ ፈረስ፤ ጠምደው ሲያርሱህ በሬ _ _ _ ስትታለብ ጥገት፤ በቁም ሲያርደህ ሙክት፤ ሲጣልልህ ውሻ - የጅ ዕባሽ ናፋቂ፤ አዳሪ ለሆዱ - ክብሩን አስነጣቂ፤ ጫንቃህ የደለበ - ለመሸከም ቀንበር፤ እንቢኝን የማታውቅ - ከእሽታ በቀር፤ እንዳህያ ጭነት - ሸክም ያለመደህ፤ ሲገፉት ነፃነት - የማይበርደው ገላህ፤ አጎንባሽ ለመጣው - የሞትክ ነህ በቁም፤ ወግድልኝ ወዱያ ጭራሽ አላውቅህም ! እንዳንተ ያለውን አገሬ አትናፍቅም::

ለም አፈርም ይሁን መላጣ፤ መረሬ፣ ኩርንችት፣ አሸዋ፣ መደበቂያ ዋሻ ፣ ምሽግ ለዱር አውሬ፣ ወይ ፈረስ ማቆሚያ፤ ግጦሽ ለአንድ በሬ፣ አልያም ለዶሮ፤ በጓሮ ማቆያ እየሰጡ ጥሬ፣ ሃገር ያው ሃገር ነው፤ አይፍቁትም ስሙን፣ አይንቁትም ክብሩን፣ ምን! ቢያወዳድሩት፤ ቢለኩት በሚዛን፤ ከአደጉት ጋር ዛሬ። (2) ሲበርድ በጉያዋ፤ በእቅፏ ታቅፋ፤ ሲርብ ጎንን ዳሳ፤ ሲጨንቅም ተጨንቃ፤ ሲያለቅሱ አብራ አልቅሳ፣ ሲደሰቱ ስቃ፤ ሲከፉ ተከፍታ፤ ሆዷን ሆድ-አስብሳ፣ ደብቃ፣ ከልክላ፣ ከጠላት ከክፉ፣ አሳዳጊ እናት ነች፤ ሌላ ማንም የለም ቢወጡ ቢለፉ። (2) ሃገር ነው፤ ወንዝ ነው፤ ለጀግናም ኩራቱ፣ አባጣ-ጎርባጣው፤ ዳገት ቁልቁለቱ። እንደ እናት ከለላው፤ እንደ እናት ምሽጉ፣ የክፉ ቀን መውጫው፤ ዘር፣ ቋንቋን ሲላጉ፤ ሥቃይን ሲዋጉ። (2) የሃገር ማንነት፤ የሃገር ትርጉሙ፣ መለኪያ መስፈርቱ፤ ተቀዳሚ ቃሉ፤ ብዙ ነው ትርጉሙ፣ ሃያል ነው ምስጢሩ፣ ንገሩን ለሚሉ። (2) የሃገር ማንነት፤ የሃገር ትርጉሙ፣ መለኪያ መስፈርቱ፤ ተቀዳሚ ቃሉ፤ በእምነት ሲተሳሰር ወንድም ከወንድሙ። (2)

ወግድልኝ ወዱያ ጭራሽ አላውቅህም ! ለወለደህ ዕዳ ላገርህ ነህ ሸክም :: ንቀት ብርድልብስህ፤ ውርደት ሆኖ አንሶላህ፤ ነፃነት ሲገፉህ - ዝም ብለህ የተኛህ፤ ጭቆና ተስማምቶህ - የማይቆረቁርህ፤ በደል የተመቸህ - ጥላቻ የማይገባህ፤ ዕንቢኝን የማታውቅ - እሺን ያስለመደህ፤ ኧረ ለመሆኑ ከወዴት ተገኘህ ?! የቱ አባት አግኝቷት - ከምን ጉድ ጸነሰች፤ የቷ እናት አምጣ - ከቶ አንተን ወለደች?! እንዳንተ ያለውን ወልዳ ከምታፍር፤ ምንኛ ደስ ባላት - ጨንግፈህ ብትቀር?!

በቋንቋ ሲዋሃድ፤ ድንበር ከድንበሩ፣ ጎሳ ከጎሳ ጋር፤ ብሄር ከብሄሩ። እጅና ጓንት ሆኖ በአንድ ላይ ሲሠሩ፣ ለአንድ አቋም ሲያብሩ፤ ለአንድ ሃገር ሲኖሩ፣ የሃገር ማንነት ያኔ ነው ትርጉሙ፤ ገሃዱ ምስጢሩ። (2) ጋራ

አላውቅህም ጭራሽ ወግድልኝ ወዱያ ! እንዳንተ ያለውን አትሻም ኢትዮጵያ !! መስከረም 4 ቀን 2005 ዓ.ም

ይነጋል በላቸው)

ድሮ የምናውቀው፣ ወጉ የሽምግሌና በደልን የሚያረክስ፣ የጎበጠውን የሚያቃና ነበር ብቃት ያለው፣ የሞራል ልዕልና። ዛሬ-ዛሬማ! ለስሙ ነጭ ጸጉር ያበቀሉ ቆብ የደፉ፣ ነጠላ ያንጠለጠሉ ስብዕናችሁን አዋርዳችሁ፣ ለምኑ የሚሉ የሽምግልና ሚዛኑን ያዛቡ፣ ጭነቱን ያቃለሉ ኧረ ምን ጉዶች በቀሉ - ተፈለፈሉ። ለጉልበተኛ ያደሩ፣ ለግፈኛ የሰገዱ ላለው እጅ የነሱ ያጎበደዱ የዘመን ውርጃ ጭንጋፎች የባርነት ጋሻ-ጃግሬዎች ክብረቢስ ለማኞች ባደባባይ መኮፈስን የመረጡ በብርሃነ-መስኮት ለመታዬት የቋመጡ ኧረ እንዴት ከወዴት መጡ። ሊያደርጉን የተነሱ ውዳቂ፣ ትቢያ፣ እራፊ የውርደት ማቅ ለባሽ፣ አንገት ደፊ ቀራፊ በዙሪያችን የተዘሩ ፍላጻ፣ እሾህ፣ አሜኬላ የሆኑብን የደህንነታችን መንገድ ኬላ ሊያሸክሙን የተነሱ የመከራ አበሳ የማይሽር የሕሊና ቁስል ጠባሳ። መሄጃ መድረሻ ሳያሳጡን ጭራሹን ሳያጠፉን ጎበዝ! ወጊዱ እንበላቸው ጥፉ ከፊታችን ይሻላልና እርዛት ጥማት እስራትና ግርፋት፣ ብሎም የክብር ሞት ትውልድ ከሚጠፋ፣ ላይመለስ አገር ከሚወድም ከዓለም ለዘላለም!!! ይነጋል በላቸው

(ኃይለጊዮርጊስ ደስታ)

ከነገሮች ሁሉ ሚዛን የሚደፉ፤ ሁለት ዓብይ ነገር፣ ወደ ላይ ቢወጡ፤ ወደ ታች ቢወርዱ፣ በዚች ዓለም ምድር፤ ተምሳሌት፣ እኩያ፣ ወደር የሌላቸው፤ እናትና ሃገር። “የኔቢጤም” ብትሆን መንገድ ዳር ኑሮዋ፣ ሰምበሌጥ፣ ፕላስቲክ፣ ከሰኔል ቢሰራ መኖሪያ ጎጆዋ፣ አልያም ንግሥቷን ዙፋን ላይ ተቀማጭ የሥልጣን እጣዋ፣ እናት ያው እናት ነች። በሌላ አይተኳትም በእናትነት ክብሩዋ። (2)

የአያት የቅድም አያት - ጀግንነቱ ቀርቶ፤ ሽለላ፤ ፉከራው - ዕምቢልታ ቀረርቶ፤ በጦር ደረት መብሳት - በጋሻ መክቶ፤ አሻፈረኝ ማለት - ለበደል ለጥቃት፤ በጀግንነት መሞት - ላገር ለነፃነት ፤ መሆኑ ቀረና፤ የጀግና ልጅ ጀግና፤ ሰብዕናህ ተገፎ - ዝቅ ብለህ ወደታች፤ ባይተዋር ያገሩ - የበይ ተመልካች፤ ውሎ ጦም አዳሪ - የሃብቱ ተመጽዋች፤ እራስክን ዝቅ አርገህ - ክብርህን ያዋረድክ፤ የት ቦታ ተዘራህ አገሬ ላይ በቀልክ?!

የሽማግሌ ያለህ!

ሁለት ዓብይ ነገር፤ እናትና ሃገር

(

ሸንተረሩ ብቻ አይደለም ሃገር ዳገት ቁልቁለቱ፣ ሕዝቦቿም “ሃገር” ነው፤ ስፋቱ፣ ልማቱ፤ በቁጥር ውልደቱ። እምነትም “ሃገር” ነው፤ ባሕልን ጨምሮ፣ አንጡራ ሃብታችን፤ የሚለየን ከዓለም “ረቂቅ-ቋጠሮ”። ሙዚዬም፣ ገዳማት፣ አፈሩ፣ ፀበሉ፣ ዋልያ፣ ኒያላ፣ የአማርኛው ቁጥር፣ መለያው ፈደሉ፣ ይሕ ሁሉ “ሃገር” ነው፤ የአንድምታ ትርጉሙ ምስጢራዊ-ቃሉ። (2) እንኳንስ ነፍስ ያለው ሕያው በአካል ቆሞ፣ “አርዲና ድንቅነሽ” የተገኙ አጥንቶች ከዚሕ በፊት ቀድሞ፣ ምስክሮች ናቸው፤ ለሃገር ትርጉሜ፤ ያስጠራሉ አገርን፤ ተለይተው ደግሞ። (2) “የኔቢጤም” ብትሆን መንገድ ዳር ኑሮዋ፣ ሰምበሌጥ፣ ፕላስቲክ፣ ከሰኔል ቢሰራ መኖሪያ ጎጆዋ፣ አልያም ንግሥቷን ዙፋን ላይ ተቀማጭ የሥልጣን እጣዋ፣ እናት ያው እናት ነች። በሌላ አይተኳትም በእናትነት ክብሩዋ። (2) ለም አፈርም ይሁን መላጣ፤ መረሬ፣ ኩርንችት፣ አሸዋ፣ መደበቂያ ዋሻ ፣ ምሽግ ለዱር አውሬ፣ ወይ ፈረስ ማቆሚያ፤ ግጦሽ ለአንድ በሬ፣ አልያም ለዶሮ፤ በጓሮ ማቆያ እየሰጡ ጥሬ፣ ሃገር ያው ሃገር ነው፤ አይፍቁትም ስሙን፣ አይንቁትም ክብሩን፣ ምን! ቢያወዳድሩት፤ ቢለኩት በሚዛን፤ ከአደጉት ጋር ዛሬ። (2) ስለዚሕ፤ ለኔ ምድር ማለት፤ ለኔ ሃገር ማለት፤ ለራሴ ትርጉሙ፣ እምነትና ባሕል፤ ታሪክና ቅርሱ፣ ብራናው ቀለሙ፣ አፈሩ፣ ፀበሉ፣ ገዳማት፣ አዝርዕቱ፣ ሰብልና ቅመሙ፣ ጋራ ሸንተረሩ፣ ወንዝና ዳገቱ፣ የብሔር ጥምሩ፣ የጎሳው ውሕደት፤ ሕብር ስብጥሩ፣ በአንድነት ልዩነት፤ ግምደት ትሥሥሩ፣ በዘርና ቋንቋ ግፊያው መቃቃሩ፣ ልዩነቱ ጠቦ፤ “ዩናይትድ-ኢትዮያ” ሕልሙ ተደራጂቶ፣ አብቦ ተውቦ፣ አንድ ሃገር፤ አንድ ቋንቋ፣ አንድ ሕዝብ በአንድ ላይ፣ ተመስርቶ ማየት ኢትዮጵያ ምድር ላይ። (2) ለዚሕ ነው፤ ሁለት ዓብይ ነገር፣ ከነገሮች ሁሉ ሚዛን የሚደፉ፣ እናትና ሃገር ረመጥ ሚሆኑት እንደዋዛ ሲያልፉ። (2) ቅዱስ ጴጥሮስ ከተማ 2004 ዓ.ም፤ ኃይለጊዮርጊስ ደስታ

ምነዋ ኢትዮጵያ…?

ፊልጶስ

እንደ ይሁዳ ከዱ፣ ልጆችሽ ሸፈጡ እንደ ኤሳው ሆኑ፣ ቡክርናቸውን ሸጡ በመታመን ፋንታ፣ ኑፋቄን መረጡ። እንደ ባህር አሸዋ - እንደ ሰማይ ከዋከብት ምነዋ ኢትዮጵያ ... በዛብሽ ጠላት? ... አፈርሽ ”ሰለሰ”፣ ሜዳሽ ”አሜክላ” እሾክ አበቀለ ተራራ ሸለቆሽ ”ጃርት” ተራባበት - ተራብቶም ፏለለ፤ ባላና ማገርሽ፣ ምሰሶሽ ተማሰ ዞብ አምባሽ ተናደ፣ ወንዝሽ ደፈረሰ ደም እንደ ጎርፍ ውሀ፣ በገላሽ ፈሰሰ ውጭ ውስጥሽ ነቀዘ፣ ቤት አጉራሽ ፈረሰ ምነዋ ኢትዮጵያ ... ምፅአት ለአንች ደገሰ? የሚታመን ጠፋ፣ ለሰው ልጅ ያደረ ውሸት ገኖ ናኘ፣ በቀየሽ ከበረ ዘብጥያ ወረደ፣ እውነትም ታሰረ ታሪክ ተረት - ተረት፣ ብስራት ተበሰረ፤ የውርጃ ”አደፍ” ቅሪት፣ ጭንጋፍ አሳድገሽ ”ቃልቻ ዘር - ጎጥን”፣ ደም ተጠማልሽ ጉድ ውልዶ ”አነበረ”፣ ግዜ ማህፀንሽ ምነዋ እናት ምድር… ያልታየ ታየብሽ? እንደ ይሁዳ ከዱ፣ ልጆችሽ ሸፈጡ እንደ ኤሳው ሆኑ፣ ቡክርናቸውን ሸጡ በመታመን ፋንታ፣ ኑፋቄን መረጡ። እንደ ባህር አሸዋ - እንደ ሰማይ ከዋከብት ምነዋ ኢትዮጵያ ... በዛብሽ ጠላት? ... በቆብ ደፊ ”ሻሻም፣ ቀሳሽ መሳይ፣ ኮከብ ቆጣሪ ” በቀን ሰባኪ፣ ማታ ጎፈሬ አበጣሪ በደብተራ፣ ረጅም ተላባሽ፣ ካባ ተሞሻሪ በዘንግ ተውረግራጊ ፣ ወገብ አሳሪ፤ ማህደረ ቅርስ ”ፅባወተ - መምበርሽ” ታምሶ በዛር ፈረስ ደመ ነውጠኛ፣ መቅደስሽ ‘ረክሶ፤ የአምላክ ጻድቅ - ሰማአታትሽ ማደሪያ ተቸበቸበቸበ ወ’ቶ ባደባባይ ደርቶ በገብያ ታበዩ በእግዚአብሔር … ምነዋ ኢትዮጵያ …? አንድ ቀን ለተለበሰ ”ጥቁር ካባ”፣ ለተደፋ ”ጥቁር ቆብ” በሚሉ ከ’ኔ ወዲያ የለም ልሂቅ፣ አዋቂ፣ ለሀገር የሚያስብ በሚመስላቸው እነሱ ብቻ የሆኑ ህዝብ፤ እየተራበ ያጠገባቸውን - እየታረዘ ያለበሳቸውን ሳይማር ያስትማራቸውን - ሳይከፍሉት የከፍላቸውን እየናቁት ያከበራቸውን - እየሞተ ያኖራቸውን በረሱት፣ በከዱት፣ የገዛ ማንነት ወገናቸውን፤ በ’ነ ከረባት … ማ’ረጋቸው በ’ነ ሆድ … አምላካቸው፤ በነሰለጠን ባይ፣ ደንቁረው አደንቋሪ ውስጠ ”አንኮላዎች” ያልሆኑትን ለመሆን፣ በመስሎ፣ ህሊና ቢስ ሸፍጠኞች በጥራዝ ነጠቅ ”ርዕዮት አለም” ሰባኪዎች ያዩትን ያላዩትን ናፋቂ፣ በብልጭልጭ ኰተት ጎታች ተሸካሚዎች የሀገር ርዕይ በሌላቸው፣ በቅዥታም፣ ተቀጥላ ጅራቶች፤ ተገዘገዝሽ! ... ተቦረቦርሽ! ... ተከፋፈልሽ! … እንደ ቅርጫ ስጋ ገነጣጠሉሽ - ቸበቸቡሽ! ምነዋ ኢትዮጵያ …………………..? ምነዋ ኢትዮጵያ …………………...? ባጠባሽ ተነከስሽ፣ ባጎረስሽ - ተበላሽ አመድ አፋሽ ሆነ፣ የዚህ ዘመን እጅሽ። እንደ ይሁዳ ከዱ፣ ልጆችሽ ሸፈጡ እንደ ኤሳው ሆኑ፣ ቡክርናቸውን ሸጡ በመታመን ፋንታ፣ ኑፋቄን መረጡ። እንደ ባህር አሸዋ - እንደ ሰማይ ከዋከብት ምነዋ ኢትዮጵያ ... በዛብሽ ጠላት? ... ወግ ነው ሲዳሩ እንዲሉ፣ ”ተማሪ” ነኝ በሚሉ ይይዙትን አ’ተው፣ ይጨብጡትን በዋለሉ በመማሪያ የብእር ደም ብልቃጥ፣ ውሀ በሞሉ፤ በኮሌጅ - ዩኒቨርስቲው፣ በየትምህርት ቤት የሚማሩት፣ የሚያገኙት የእውቀታቸው አይነት የአድማሳቸው ልእልና፣ የ’ርካታቸው ጥማት የወጣትነት ህይወታቸው፣ የጥበባቸው እድገት፤ አባትን ሳያውቁ፣ አያትን መጠየቅ ሱሪ በአንገት ማጥለቅ፣ በጎጥ እድር መድረቅ፤ ዲስኮ … ጫት … ሀሽሽ ”ፓሪ” መንጎድ ምነዋ እናት ሀገር …. ምነው ጠፋ ትውልድ። እንደ ይሁዳ፣ ከዱ ልጆችሽ ሸፈጡ እንደ ኤሳው ሆኑ፣ ቡክርናቸውን ሸጡ በመታመን ፋንታ፣ ኑፋቄን መረጡ። እንደ ባህር አሸዋ - እንደ ሰማይ ከዋከብት ምነዋ ኢትዮጵያ ... በዛብሽ ጠላት? ... ርሀብ - እርዛት፣ ሰቆቃና ስደት ስም መጠሪያሽ ሲሆን፣ አንች ባለሽበት፤ እርስ በርስ መባላት፣ ትውልድን ሲጨርስ የፍትህ ያለህ ባይ፣ ዓለምን ሲያዳርስ፤ ወገኑን - ወገኑ፣ ገሎ ሲፎክር ሀውልት ሲገነባ፣ በአንች ምድር አፈር ምፃ’ተኛ ‘ሲኮን’፣ በገዛ ሀገር፤ ጥቂቶች ሲስቁ፣ ብዙሀን ሲያለቅስ ኃጢአት ተትረፍርፎ፣ ፅዋው ሞልቶ ሲፍስ ዘመን አልፎ ዘመን፣ ዛሬም ደም ስናፈስ ምነዋ ኢትዩጵያ …………………? ምነዋ እናት ምድር … ዝም አለ የአ’ች ነፍስ? ፍርድ ስጭ ዝም አትበይ፣ ተይ አትታበይ ዋጋ ይከፈለው፣ በዳይ - ተባዳይ

ይቅርም አባብይን፣ ወደፊት እ’ድናይ። … የነፃ ህዝብ መልኩ ሰንደቅ አላማቸው ባላደራ እናት ነሽ ቅርስ ያ’ርነታቸው። አለሁ ካልሽ አለው፣ በይ መስክሪ በራስሽ ከአንገቱ ተቃንቶ፣ ማየት የሚሽ ይይሽ። … ”ያላያ ኢትዩጵያ … የለሽም - እያለሽ የጀመረሽ ምፅአት፣ ፍፁም ይጨርስሽ ፀሀይ ከጨረቃ፣ ይጨላልሙብሽ ከዋከብት ይርገፋ፣ ሰማይ ይደፋብሽ እሳት ገሞራ፣ ይንደድ በላይሽ፤ ከምድር ገፅ ላይ ጠፍቶ ‘ምስልነትሸ’ ሲኦል ውረጅና ከነ-ግሳግስሽ ዓለም ታሪክ ይፃፍ፣ እፎይ ይበልልሽ።” -----//-----ፊልጶስ /በመጨረሻወቹ ስንኞች ምን ለማለት እንደፈለኩ፣ ወድ ኢትዮጵያዊያን እንደምትረዱልኝ እምነቴ ነው።/ ለአስተያየት በኢሜል፡ philiposmw@gmail.com

TZTA INC

TZTA INTERNATIONAL ETHIOPIAN BILINGUAL NEWSPAPER TZTA is independent newspaper published once a month in Toronto, Canada. The opinion expressed in this newspaper are not necessarily those of the editor or publisher. We welcome comments or different point of view from our readers submitted articles may be edited for clarity.

Address

Send your article, letters, poems and other information with your full name, address and phone number to:-

TZTA INC. 851 Bloor Street West Toronto, ON M6G 1M3 E-mail your information to:tzta@sympatico.ca Website:www.tzta.ca SUBSCRIPTION One year subscription 12 Issues in Canada and outside Canada $12.00. Prices are not included GST. GST REG. # R306528806-00001

PAYMENT

Make your cheque payable to TZTA INC. For residence of Canada cheque and money order are acceptable. From outside Canada only money order are acceptable. Receive your next edition of TZTA by subscribing now.

For Advertising

Call office; (416) 653-3839 Cell: (416) 898-1353 Fax: (416) 653-3413 E-mail: tzta@sympatico.ca Website: www.tzta.ca Publisher & Editor Teshome Woldeamanuel Marketing; Tigist Teshome Format and Typing Zenashe Tsegaselassie Contributor Mr. Tadese Gebremariam Mr. Yonas J. Haile Mr. Samuel Getachew etc...


ደብዳቤዎች

የቶሮንቶ በረከቶች ምን ይላሉ?

አሁንስ ቁርጥ መብላት አስጠላኝ አለች አሉ ብዙ! ከጋዜጠኝነት እስከአሁኑ የሰደት ዘመኗ ባበረከተችውና በማበርከት ላይ ባለቸው ቅን ህዝባዊ አገልግሎት እጅግ የምረካባት በፓልቶክ መጠሪያዋ ሙያየ ምስክር ነች አሉ ባንድ ወቅት ይህን ያለቸው። እውነት ቁርጥ ጠልታ ላይሆን ይችላል፡ ከቁርጡ ጋር የተነካኩት በጣም ጥቂት ሰዎች በጸረ ወያኔ ትግል ስም ጸረ ወያኔ ሰባዓዊ መብት ተከራካሪዎች ላይ የሚያዝጎደጉዱት ስድብና ስም ማጥፋት ተማራ እንጅ። ይህን ጽሁፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝና ርዕስና መንደርደሪያ እንድሰጥ የገፋፋኝ ባለፈው ኦገስት የወጣች ትዝታ ጋዜጣ ነች። ጋዜጣዋ አንባቢ ይፍረደኝ በሚል ለእውነት ስለእውነት የተማጽኖ ጥያቄ አቅርባለች። የበኩሌን ማለት እችል ይሆን ብየ ራሴን ጠየቅሁ። አዎ ውሸት ተውገርግሮ እያዩ ዝም ማለት የውሸቱ ተካፋየ ያሰኛል አልኩና የምለውን ለማለት ወሰንኩ። ያለፈው የኦግስት ትዝታ እትም ካንድ ድርጅት ፕሬዚዳንት ነኝ ባይ የተፈረመ ደብዳቤ አስፍሯል። ይህን ጽሁፍ ማውጣታቸውም ሆነ ስለነጻ ሚዲያ ምንነት በመዘርዘር መልስ በመስጠታቸው አታሚውን አመሰግናቸዋለሁ። በማሳሰቢያና በማስታወቂያ የተሞላው ይህ ጽሁፍ የጸሃፊዎችና የፈራሚውን ማንነት ከማሳየቱ በላይ ለነጻ ሚዲያና ሃሳብን የመግለጽ ነጻነት ምን ያህል ንቀት እንዳላቸው ያስረዳል። እነሱ ህግ አዋቂዎችና ተርጓሚዎች እንዲሁም አስፈጻሚዎች አድርገው በቆጠሩበት ኮሚኒቲ ውስጥ የግለሰቦችን ሃሳብ የማንሸራሸር ህጋዊ መብት እንዲገደብ ማስጠንቀቂያ ለጋዜጣ አዘጋጁ መስጠት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሚዲያ አሰራርና አስተዳደር ያስታውሰናል። በካናዳ እየኖርን እንደ ኢትዮጵያ እንተዳደር የሚል ምርጫ ያለ አይመስለኝም፡፡ በኢትዮጵያ ሚዲያ ህግ መተዳደር ከፈለጉ ድርጅታቸውን ይዘው ወደዚያው መንጎድ ይችላሉ። ሚዲያ እንዲታፈንላቸውም ብቻ ሳይሆን የፈለጉትን ማሳሰርና ማስገረፍ በመከረኛይቱ ኢትዮጵያ ይቻላልና፣ ጉዋዛቸውን ጠቅለው ቢነጉዱ ለነሱም ለኛም የተሻለ እንደሚሆን የበኩሌን አሳስባቸዋለሁ። እነዚህ ግለሰቦች ተጠያቂነትን የሚያነሳ ጽሁፍ ለምን ይወጣል ከሆነ ከተጠያቂነት ነጻ የሚያደርጋቸውን ማስረጃ በጽሁፍ ለኮሚኒቲው ማቅረብ እንጅ የሚዲያን ተግባር ማደናቀፍ እንደ ኢትዮጵያ እያሰቡ በካናዳ ለሚኖሩት ማናለብኝነት ፈጽሞ አይሰራም። ከስድስት አመት በፊት መሆኑ ነው እነዚህ ግለሰቦች ቡድናቸው ውግርግሩ ወጥቶ በተለይ ቶሮንቶን ወደ ሁለት ዋና ጎራዎች የከፈሉ፣ ህጋዊ ተወካይ እኛ ነን ብለው እስከ ፍርድ ቤት በደረሰ ተማጽኖና ከፍተኛ ወጭ በሌላው ወገን ላይ ከክስም ባሻገር ሁለገብ ዘመቻ ማካሄዳቸው የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው። ሁለቱም ተፋላሚዎች የቀጠሯቸው ጠበቆች ባሳሰቡት መሰረት ክሱ ከፍርድ ቤት ውጭ ያልቅ ዘንድ ተፋላሚዎች እንዲስማሙ አግባብተው የጨረሱትን ውሮ ወሸባየ ዳንኪራ መተውበታል። ከግዳጅ መልሰ በድል የተመለሰ ሰራዊት የሚሰጠውን መግለጫ ነበር ላፍቃሪ አደሀሪ ጌቶቻቸው የረጩት። ማቸነፍስ ልብ ነበር እንዳሉት ፕሮፌሰር መስፍን ግምቱ $30000 የሆነ በርዳታ የተሰበሰበ ገንዘብ ለጠበቆች ሲሳይ ካደረጉ በኋላ ዳንኪራው ማን ለማሞኘት እንደሆነ የሚያብራራ Toronto off leash again በሚል አንድ ጽሁፍ በትዝታ

መውጣቱ ትዝ ይለኛል። ያን ጽህፍ አስከትሎ ነበር ይህ የውሮ ወሸባየ የአትንኩንና ከኛ በላይ ላሳር ቡደን ትዝታን ዋ ዳግመኛ እኛን የተመለከተ ጽሁፍ ብታወጣ ወዮልህ ብለው ያስጠነቀቁት። ባደባባይ ለህዝብ ሞነጫጭረው ያስነበቡትን ጽሁፍ እንዴት ቃል በቃል እንዳለ በጋዜጣህ ታወጣለህ የሚሉም ግለሰቦች ከዚያው ቡድን ውስጥ ተካተዋል። ስንቱ ይታረማል እንጅ አርሞ ባያወጣው ኖሮ ሊደርሰበት የሚችለውን ቁጣ እኛም ለማንበብ የሚወስድብን ጊዜ በጅጉ ባሳጠርን ነበር። አንዳንዴ ሳስበው የእነዚህ ሰዎች ተግባር በረከት በነጻው ሚዲያ ጋዜጦች ላይ ያደረጋቸውን ድንፋታዎች ያስታውሱኛል። አቶ በረከት የሟቹ አምባገነን ቀኝ እጅና ሚስጥረኛ እንደሆኑ ይታመናል። አምባገነኑ መሪ በኢትዮጵያና በህዝቡዋ ላይ የፈጸሙአቸው ሰቆቃዎች ሁሉ አቶ በረከት ከጎን ባስፈጻሚነት ተሳትፈዋል። በተለይም ከመቶ በላይ ለሆኑት ነጻ ጋዜጠኞች ሞት እሰራት እንግልትና ስደት አቶ በረከት ዋና አስፈጻሚ ናቸው። አንዳዶች አቶ በረከትን ከሂትለሩ ፕሮፓጋንዳ ሚኒስተር Joseph Goebel ጋር ያመሳስሏቸዋል። በየዎቅቱ በተቃዋሚዎችና በጋዜጠኞች ላይ የሚቀርበውን ድራማ የሚያቀነባብሩት አቶ በረከት እንደሆኑ ግልጽ ነው። ለሂትለርም Josep Goebel እደዚሁ ተቃዋሚዎችን ለማጥፋት እንደ አኬል ዳማ ይጠቀም እንደነበረ ታሪክ ያስተምረናል። አቶ በርከትና በፍጹም ታማኝነት ያገለገሉዋቸው አምባገነን ህዝቡን በፍርሃት ተሸማቆ እንዲኖር ሲሉ ያልተጠቀሙበት የፕሮፓጋንዳ ስልት አልነበረም። ሁለቱም እንደዋናና እንደ ረዳት የገዟት ኢትዮጵያ ውስጥ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያው ሁሉ ፍጹም ውሸትን ሲያመርት እንደነበረና መከራው ያላባራው ህዝብ እውነትን እኩልነትን ሰላምና ብልጽግናን ሊመጣለት እንዲችል የዘወትር ፍላጎቱና ጸሎቱ ነው። ቅጥፈት በደማቸው ውስጥ አለ ይባልላቸው የነበሩት አምባገነን ታዓምራዊ በተሰኘለት መልኩ ከዚህ አለም ሳይታሰብ ተለይተዋል። አዲሱ መሪ እንደቀድሞው አገሪቷን በውሸት ይመሯት ይሆን? እናያለን። ከ Josep Goebl እና ከኢራቁ ሙሃምመድ ሴኢድ አል ሻሪፍ የሚመሳሰሉት አቶ በረከት የተካኑበትን አፋኝ ተግባር በአዲሱ አመራር ይቀጥሉበታል ወይ እንደ ሟቹ ጓዳቸው ክፉ ባህሪ እስከመቃብር ነው ይባላል? ወደተነሳሁበት ቁም ነገር ልመለስና ትዝታ ጋዜጣ አሳታሚው እንዳሉት ለኮሚኒቲያችን እንድ ብቸኛ የሃሳብ መለዋዎጫ መጠቀሚያችን ነች። በዚህ ረገድ ከፍተኛ አገልግሎት እየሰጠች ለመሆኑ በርካታ ማስረጃዎች አሉን። ይህን አገልግሎት ለማደናቀፍ የሚደረግን ሙከራ ህብረተሰቡ ሊቃወመው ይገባል። 17 ዓመት ሙሉ ግልጋሎት የሰጠን ጋዜጣ የግለሰብና ቡድን ፍላጎትን ባለሟሟላቱ ሊወገዝ ይገባዋል? ከላይ የተጠቀሱት የድርጅት መሪ የላኩት ደብዳቤ በአጠቃላይ ይዘቱ ሲታይ የጋዜጠኛውን ሙያ የሚጋፋና ብቸኛዋን ጋዜጣ ለማዘጋት የፈለጉ ይመስላል። ይህ ባይሆን ኖሮ ግልባጭ ለተለያዩ ድርጅቶች መላኩ ባላስፈለገ ነበር። ቶሮንቶ እንደበርከት ለሚያስቡና ለሚሰሩ ግለሰቦች ሳይሆን መቻቻልን፤ መፋቀቃርን፤ መከባበርን፤ ቅንነትን፤ እኩልነትን የህግ የበላይነትንና ነጻ ሚዲያን ለሚሰብኩ ሁሉ መሆን አለባት። ደብዳቤ ገጽ 11 ይመልከቱ ይሁን በላይ ከቶሮንቶ

TZTA: Page 9: October 23, 2012 : www.tzta.

For your eye or eyeglasses needs we are here to help. Our well trained staff members with years of experiences could answer your questions and help or assist you with your new purchase or old glasses fixings or fittings. We are a call away please reach us by phone, e-mail or pay us a visit. F0r further information call:

Phone :

416-960-3223 * Fax: 416-960-3227

464 Parliament St., Toronto, ON M5A 3A2 www.facefurnitureoptical.com info@facefurnitureoptical.com

SHAWN

FORK LIFT Driving School

ለፎርክ ሊፍት ላይሰንስ ለማውጣት የምናስከፍለው

$75.00ብቻ ነው።

አስተማሪዎቹ ፕሮፌሽናሎች ናቸው። በሳምንት 7 ቀን ክፍት ነን። ጎብኙን ስልክ ደውሉልን።

Tel:-416-297-5435 * 416-829-0603 60 Nugget, Unit 9, Scarborough, ON

DH AUTO SERVICE Specialaized in Auto Repair St

Domestic & Import

ማንኛውንም መኪና እንጠግናለን፤ መኪናም እንሸጣለን። አዲሱን አድርሻችንን በተደራጀ መንገድ መጥታችሁ ጎብኝን። Tel:-

416-832-7064

1705 Wesston Road Unit #9 Toronto ON


TZTA: Page 10: October 23, 2012 www.tzta.ca

COMMUNITY CLASSEFIED DIRECTORY ACCOUNTING

የሂሳብ ሥራና ታክስ DISCOUNT INCOME TAX SERVICE

BEAUTY SALON & SUPPLY BEAUTY SALON & SUPPLY BEAUTY SALON & SUPPLY የውብት ሳሎን የውብት ሳሎን የውብት ሳሎን

Mona-Lisa UNISEX

1179 Bloor Street West , Toronto, ON የድሮ አድራሻችንን ቀይረን ለአዲስና ለደንበኞቻችን 1179 በብሉር ስትሪት ዌስት ቶሮንቶ መንገድ ላይ በመክፈት ቤታችንን ሰፋ አድርገን ደንበኞቻችንን እንጠብቃለን።

Tel:- 416-531-0073

416-530-0247

ACCESSORIES & ALTERATIONS SERVICES የልብስ ስፌትና ፋሽን

የኢትዮ-ልብስ ስፌት

Ethio-Sewing

2009 Danforth Avenue Toronto, ON (Near Woodbine Subway)

ከኢትዮጵያ ማሕበር ጽ/ቤት አካባቢ

For more information call Stylist: Sofia at:

BEAUTY SUPPLIES SALON SELAM

ሰላም የውበትና ፀጉር ሥራ

* Hair color and styling * Highlightening & Coloring * Relaxer * Twisting Straightening * Weave Braiding *etc... Tel:-

647-340-0075

We do Alterations on the old or latest fashion.

የዘመኑን ፋሽን የተከተሉ የሃገር ባህልና ድንቅ ልብሶችን እናዘጋጃለን። የሚዜ ልብሶች እንሰፋለን። የተዘጋጁ የሐበሻ ልብሶች እንሸጣለን። በአዲስ መልክ የሚሰፉ ልብሶችን እናስተካክላለን።

Tel: 416-816-1126 E-mail: ela1623@yahoo.ca

MORTGAGE

INVIS MORTGAGE BROKERAGE 2610 Weston Rd. Unit #206

Brokerage Lic. 10801 / Lic. M090022232

አቶ ዮሓንስ ላሞሬ

Cell:-

416-576-0055

905 Bloor St. W. of Ossington Ave. AUTO Repairs and Sale (Used cars)

የአውቶሞቢል ጥገና እና ሽያጭ JAMAL’S AUTO REPAIRS 185 Weston Road, Toronto, ON Domestic & Imported

Cars Repairs & Maintenance

*Residential and Business Loan * Line of Credit * Over 40 Lenders

ያገር ውስጥ ሆነ የውጭ መኪናዎችን በአስተማማኝ ዋጋ እንጠግናለን፣ እንሸጣለን። በቅናሽ ዋጋ ወደ ጨረታ ቦት እንወስዳለን።

ብድር ለቤት ግዥና ለማንኛውም ቢዝነስ ለማግኘት ለዮሐንስ ላሞሬ በመደወል ደውለው ይረዱ።

Tel: 416-604-4553

416-854-4409

Vedio Services

የቪዲዮ አገልግሎት

*Wedding *Birthday *Enqagement *Baptism

TEKMEK PHOTOGRAPHY

*Social Funct

For more information call Mekonnen

647-207-2622 tekmck2006@yahoo.ca

10 GatewayBlvd. Unit #R160Toronto, ON, M3C3Z6

JKTO12&University MATH–ENGLISH–SCIENCE- ALLSUBJECTS ONTARIOQUALIFIEDTEACHERS FOLLOWONTARIOCURRICULUM AFFORDABLERATE HOME WORKHELP 100 %GRADE IMPROVEMENT INDIVIDUALATTENTION

CALL:416-879-4706

Tel: 647-868-0160 Monday - Saturday 10 am - 8:00 pm Experienced for several years

HORIZONS TRAVEL INC.

*Weaves *Perms * Coloring *Relaxes *Style Cut * Hair repirs *Wigs *Waxing *Facials *Make Up *Jewelry *Professional Services * Professional Products and so much more. Professional Guidance for : Hair Care - Cosmetics - Personal Care.

Call ሮማን At:

416-781-8870

Financial Services የገንዘብ ሥራ አገልግሎት 300-245 Fairview Mall Drive Willowdale ON

Yesuf Abdulmenan

Bus. 416-493-9560 Cell: 416-948-2163 E-meil:yusuf.abdulmenan@sunlife.com

Production

የሠርግ፤ የቀለበት.የልደት፤ የሌሎቹም ዝግጅቶች እንቀርፃለን! ሊሞዝን ሲያስፍልግዎ ሳሚን ስልክ ድውላችሁ ጠይቁ። Services for your video need: *Photo printing from video clips * Overseas video conversion *Mass DVD/VHS/CD duplication *VIDO to DVD * Smm/ mini DV/VHS/DV CAM to DVD We provide luxury limousine service

416-824-6151

video.sammy@gemail.com

Ali Salih, Manager

Tel: 647-347-0444 Fax: 647-347-1623 505 Danforth Avenue, Suite #202 E-mail: horizonstravel@rogers.com

851 Bloor Street West, M6G 1M3 When planning your trip call us first @

416-535-8872 በኛ በኩል ስትጓዙ ፀሐይ ለፀሐይ ነው መንገዱ

www.sunlife.ca/yusuf.abdulmenan

Lawyer/

Computer Sale & Repair

1600 Eglinton Ave W, York, ON

Computer Sale & Services We are offering FREE Consultation & Evaluation

Tel:- 416-782-5959

SAMMY VIDEO

ለማንኛውም የጉዞ አገልግሎት ፍላጎትዎ አሊ ሁሴንን ያነጋግሩ።

አቶ የሱፍ አብዱልመናን Worldwide Travel

Printing and Art ሕትመትና የፈጠራ ጥበብ

Tel: 416-654-2020

416-654-1406

1722 Eglinton Ave. W, Toronto, ON ፀጉር በስታይል እንሰራለን። በደድሊይ ፕሮዳክታችን እንታወቃለን።

*Internet Cafe * Upgrades * Repairs * Virus Removal

inviation

Hair Stylist ፀሐይ

TRAVEL AGENT/የጉዞ ወኪል

Cell: 416-554-1939 Tel: 416-537-4063

633 Vaughan Rd. Toronto Complete Printing and copy servicesi ncluding wedding

(የቁንጅና ሳሎን)

ROMAN`S `N CARE

DUDLEY`S Beauty Centre

Mice @ Work Inc

E-mail:tana@rogers.com Website: tanaprinting.com

DonMills TutoringService

መረጃ ገነት ራዲን ስልክ ደውላችሁ ጠይቁ።

Early Booking for G1 & G2 Road Test

TANA PRINTING ጣና ማተሚያ ቤት

*Curls *Color *Weavers * Relaxers *Braids *Cuts etc...

የወንዶችና የሴቶችን ፀጉር በፈለጋችሁት ስታይል አስምረን እንስራለን። ለማንኛውም

የኮምፑተር እደሳትና ሽያጭ

Mohamed Adem

All Beauty Supplies Hair Accessories Specialized in Ladies and Men Hair Cuts

(at Sharebourne)Toronto, ON

Driving Instructor

መኪና ያስተማርኳቸሁ ሁሉ ተሳክቶላቸዋል።

534 Oakwood Ave. Toronto, ON

243 Queen St. E.

ለማንኛውም ጀማል ብላችሁ ስልክ ደውሉልን።

DRIVER INSTRUCTORS የመኪና መንዳት አስተማሪዎች

SUPERIOR BEAUTY SUPPLY & SALON

Unisex

Hair Salon

YEAR ROUND 870 Bloor Street West, Toronto, ON. * Accounting * Bookkeeping * US return* Instant Tax Return Ermias Abraha

Fax: 416-531-0073

Rady Hair Salon

ጠበቃ

አቶ ዳንኤል ደጋጎ

ጠበቃ

For Info. Call: Ben Aregawuy

አበሻ ልብስና ምግብ ማርታናት ሐበሻ የሐገር ልብስ እና ምግብ አዘጋጅ

* የሐገር ባህል ልብስ ፣ ቅመማ ቅመመ እንሸጣለን። * ለሠርግ፣ ካባና የሐገር ባህል ልብስ እናከራያለን። * በልዩ ትዕዛዝ የተለያዩ ዕቃዎችን እናስመጣለን

* የምግብ ማሞቂያ፣ ብረት ድስት የጋዝ ምድጃና የጠረቤዛ ልብስ እናከራያለን።

For more

information:

416-269-5045 Cell:-647-869- 2382 Tel:-

190 Linden Ave.,Toronto,

ON M1K

FOOD STORE LIYU WHOLE 10 Howard St.

ልዩ የምግብ መደብር

ገንዘብ ወደ አድስ አበባና አሥመራ ሌሎችም አገር እንልካለን! ከኢትዮጵያ የመጡ በርበሬ፣ ሽሮ፣ ቅመማ ቅመም፣ ድርቅቆሽ ሚጥሚጣ፣ አዋዜ፣ሜኬዐለሻ፣ ክ፣ምሥር፣ ቅቤ ጤፍ፣ ግብስ፣ሰርፕራይዝዚንግ፣ የመሳሰሉትን እንሸጣለን። የኢትዮጵያ ዘፈን፣ በካሴትና በቪዲዮ ይኖረናዐል።! የተለያዩ የአማርኛ መፀሐፍቶች እናከራአለን። ከኢትዮጵያ ማንኛውውንም እቃአ እናስመጣለን። እንጄራዓ፣ ቡናዓ ቆሎ የመሳሰሉት አሉን! ኑናዓ ጎብኙን

416-922-4174 *Cell: 416-830-4174

Restaurants/Bar/Cafe ምግብ ቤቶች

ABBYSSINIA CAFE & RESTAURANT

735 Bloor St. W. Toronto, ON We prepare Abbyssinia Tibs, Aged Meats, Vegeterian Food, Seafood etc... ለክርስትና፣ ለምርቃት፣ ለልደት 30 እንግዶችን እናስተናግዳል። ቅዳሜና እሁድ አስደሳች ባንድ አለን\; ጎብኙን ስልክ ደውሉልን።

Tel: 647-344-2110 Cell: 647-703-9098 TZTA INC

TZTA International Newspaper 851 Bloor St. W. Toronto, ON M6G M1C Office: 416-898-1353 Cell: 416-898-1353 Fax: 416-653-3113

E-Mail: tzta@sympatico.ca

Website:tzta.ca * www..face.com


ማህበራዊ ጥይፍታ

ድብዳቤ ከ9 ገጽ የዞር

(Social Stigma) ከ

“Socila Stigma is......Stigma may attach to a person who differse from social or cultural norms.” ይባላል። “Socila Stigma is......Stigma may attach to a person who differse from social or cultural norms.” ይባላል። Wikipedia, the free encyclopedia.

ጋሼ ደስታ ከቶሮንቶ በሚስት፣ በልጆች አክብሮቱ ባህሪይ ይገለጻል። ሰው በታማኝነት ባህሪው ይገለጻል።.....ወዘተ በማለት የመድምደሚያው ማረጋገጫው አቀረበልኝ።

ከዚህ ሁሉ ካፈነገጠስ? ብዬ ከመጠየቅ እራሴን ሳልገድብ ጠየኩ። ታዲያ ወዳጄ አልሰለችም። በድጋሚ ስማ አለኝ “ማፈንገጥም” አለ አለኝ። የሰው ልጅ በመደለቡ ወይም በመጠብደሉ ቀጠለና የሰው ልጅ ባህሪ አንድ አይምሰልህ! ወይም የአዕምሮ በሽተኛና ዝግምተኛ በመሆኑ ሰው አንድም ሁሉትም ከዚያ በላይ ባህሪ ይዞ ወይም የስጋ ደዌ ሕመምተኛ በመሆኑ መጓዝና መኖር ይቻላል አለኝ። እንዴት? ብዬ የማህበራዊ ጥይፍታ ነው ብሎ መደምደሙ ጠየቁት። ምስጢሩ የግሉ ነው ብለሃል። ሰው ስህተት ይሆናል። በደብቅ አዕምሮ መኖርና መጓዝ የሚችል እንሰሳ ነው። የውሸት ኩሩም ነው። ስው በሌላም መልኩ ቤተ ሰብ የህብርተሰብ መሠረት የአዕምሮው ድብቅነቱን ቁልፍ መክፈቻ እራሱ ሆኖ ከታመነበት ወይም ማህበረ ሰብ ለራሱና ነው። ሰው የማህበረ ሰቡ ሕግጋት የሚጥስ ለህብረተሰቡ አግባብ ናቸው በማለት በጋራ ነው። ሰው ሰው ገዳይ ነው። ሰው ሁለት ሦስት ስምምነት በባህሉ፣ በቋንቋው፣ በማህበራዊ ከዚያም በላይ አፍቃሪ ነው። ስው ለሰው ኑሮው በሥራው የሚታገዝበትን መመሪያና መደሐኒትና አጥፊውም ነው ወዘተ....በማለት መተዳደሪያ ደንብ በማውጣትና ለደንቡም ወዳጅ አጠገበኝ። አሁንም ጥያቄዬ አላበቃም። ተገዢ በመሆን የሚከባበርበት፣ የሚወቃቀስበት ወዳጄም አልሰለቸኝም። ታዲያ የዚህን ዓይነት ማህበራዊ ጥይፍታ ሊሆን አይችልም። ሰው ድርጊት ምን ትለዋለህ? አልኩት። ወዳጄ ትኩር ብሎ ተመለክርተኝ። ቀና ብዬ ለሱ ስጓጓ በአንፃሩ ከመህበረ ደንብ ውጪ የሚሆኑትን አሁንም በዝምታ አትኩሮ ይመለከተኛል። አፀያፊ ናቸው ማለት ይቻላል። ለምሳሌ ምነው? ምን ሆነሃል? አልኩት። እያነበብኩህ ከውሸት ዓረፍተ ነገር ብንነሳ ውሸት ዓረፍተ ነው አለኝ። “ሰው ነህና ሰለሰው በአዕምሮ ነገር ላይ በመደደሚያነት እንደርሳለነ እንጂ ያዘልከውን ሸክም ወዴት ለማድረስ እንዳቀድክ ዕውነት ዓረፍተ ነገር ላይ አንደርስም ማለት ምስጢሩን እያነበብኩ ነው” አለኝና “ደግ ነው ነው። ለምን? ከመነሻው ውሸት በመሆኑ ነው። ቀጥልበት። አትቁም። ሸክምህ ለማህበራዊ ኑሮ ትምህርታዊ ነው።” አለኝ ወይም ባለሙያነት በአንድ ማህበረ ስብ ውስጥ የሚኖር ቤተሰብ አልኩኝ። በልቤ ወዳጄ ለመሆን ቃጣው። በማህበረ ሰቡ ውስጥ የሚኖር ቤተሰብ ቆይ አልኩት። ምነው? ምን ቀረህ አለኝ? በማህበረሰብ ውስጥ የተጓዘበትን የህይወትና ለጠየቁህ ጥያቄዬ ምልስ አልሰጠኸኝም የማህበራዊ ጉዞውን በተመለከተ ዕውነተኛ አልኩት። አሁንም ትኩር ብሎ ተመለከተኝና ወይም ጥይፍታዊ ታሪክ መኖር ስለሚችሉ “ሸክምህን፣ ጉዳትህን፣ በደልህን፣ ክደትህን እንደ አፈታሪክ ሆኖ እንዳይቀር በማህበረ ሰቡ አመልካች ነው። እውነተኛ ታሪክ ተሸክመሃል፣ ወይም ግለሰቦች ተመዝግበው መቀመጥም ለጥያቄህ መልስ “በማህበራዊ ጥይፍታ “ብለህ ይኖርባቸዋል። እንደየ ዓይነታቸውም አርእስት ሰጠውና ሽክምህን ለንባብ አብቃው” እንደተተኪው የማህበረ ሰቡ አባላት አለኝና አሁንምበአንክሮትና በሃዘን መልክ ለመቀበልም ስለመቀበልም ከሚያደስበት ተመለከተልኝ። ምነው ያዘንክ ትመስላለህ? መደምደሚያ ላይ ይደርሳል። የእኔ ጥያቄ ነበር። ወዳጄ ስማ አለኝ። እናቴ ዐፈር ሳትቀምስ መድብ ላይ ተጋድማ፣ እኔ በማህበረሰቡ ውስጥ የኖሩ ግለሰቦች ብዙ ከመደቡ ሥር ተቀምጬ የእናት ፍቅሯን የተለያዩ ባህርያትም አላቸው። በተፈጥሮ ስትገልፅ ፀጉሬን እየደባበሰች እንዲህ እያለች የሰው ስራ ከዕእምሮው ውስብስብ (complex) ታጫውታኝ ነበር። ``ሰውዬው የሰው ሚስት በመሆኑ ይህ ነው ተብሎ በጥድፊያ መደምደም ይወዳል። ሴትየዋም የዓይን ፍቅር ይዟታል። ያዳግታል። ከብዙ ጥናቶች በኋላ እገሌ ወይም መነጋገር አልቻልኩም። መገናኘት አልቻሉም። እገሊት ባህሪው ውይም ባህሪዋ እንዲህ እንደእናንተ ጊዜ ደብዳቤውና መገናኛ ዘዴው ከሚባለው..... ዘርፍ ይመደባል በማለት አልነበረም። ስለዚህ እንዴት ሊገናኙ ይችላሉ መደምደሚያ ላይ ሊደርስ የሚችል ይችላል። ብለህ ታስባለህ? ጥያቄ ለእኔ አቀረበች። የሥነ ልቦና፣ የዕምሮ ባለሙያዎች በአብላጫው እናቴ እኔ አፍላ ጎረምሳ መሆኔን ስለምታውቅ የግለሰቡን ባህሪ ይለዩታሉ። የባህሪውንም ዝም አለች። እኔም ውዲያውኑ የጀመርሽውን ዓይነትና መነሻ ማወቅ ብቻ ሳይሆን ጨርሽልኝና በኋላ እመልስልሽለሁ አልኳት። መፍትሄውንም ያክሉበታል። እናቴ የእኔን ሁኔታ ስሜት ፈልጋ ስለነበር ጨዋታውን ቀጠለች። መገናኛ እንዳሁኑ እኔ በንዲህ ዓይነቱ ባልሙያነት ባልታደልም ባልተስፋፋበት ወቅት መገናኛው ሰው በሰው በገጠመኝ ወይም ባሳለፍኩት የህይወት ጉዞ ነበር አለችኝ። ፍቅር መንገድ አያጣም። የግለሰብን ባህሪ ከረዥም አብሮ የመኖር የተነሳ ያውም ሁለት ያፈቀረ! ስለዚህ ሰዎች መገናኛና እንደሚከተለው ማስቀመጥ ፈለኩ። የሰው መላላኪያ ዘዴያቸው፣ ሕጻን ልጆችን ነበር ልጅ ብርቱ ነው ብዬ ጀመርኩ። መንፈሱም አለችኝ። እንዲህ እንዳለ፣ ባል ለሥራ ወደ ጠንካራ ነው አልኩ። ህሊናው ምስጢር ነው ሐረርጌ መሄድ። ሚስት ዘዴ መፍጠር። አልኩ። ምስጢሩ የግሉ ነው አልኩ። ቀጥየም የተለመደውን ሕፃን በፍጥነት አስጠርታ አሁኑኑ አንድ ሰው ዕውን አንድ ነውን? ብዬ እራሴን ሄደህ እንዲህ በለው ብላ እየደጋገመች ሕፃኑንን ጠየኩ፣ ለባለሙያነት ስላልታደልኩ፣ አዎ! ልጅ ማስጠናት ጀመርች። ``ይህን ሕፃን ልጅ አንድ ሰው አንድ ነው። በመንፈስም፣ በሥጋም፣ ከምታመላልስብኝ ሦስት ራብዕ ፈደል ቆጥርህ በባህሪም ብዬ ወሰንኩ። ግን አንድ ሰው ድረስብኝ`` ብለህ ንገረው። ብላ ላከችው። በባህሪው ሁለትና ከዚያ በላይ ሆኖ ቢገኝስ? እኔ ተሳስቻለሁ ማለት ነው። ቀጥዬ አንድ ወዳጄም ሳምንት ስንገናኝ አንተ ባለ ሙያ ሁነህ ሰው ሁለትና ከዚያ በላይ ባህሪ እንዳለው ምን የረዥም የእራስህንና የቤተሰብህንና የሕይወት ማረጋገጫ አለኝ? ብዬ መጠየቅ ተገቢና መልስ ታሪክ ጉዞና እንዲሁም ሦስት ራብዕ`` ፊደሎች የሚሻ ጥያቄ መሰለኝ። ታዲያ አንድ ወዳጄ እኔ እነማን እንደሆኑ ታወጋኛለህ። ሌላ ወዳጅ መልስ ልስጥህ አለኝና “ሰው ተግባሩ ብዙ ነው። ይጠብቀኛል በማለት ተለየኝ። ተግባሩ ባህሪውን ገላጭ ነው” አለኝ። ቀጠለና ሲሆን አለኝ። ”ሰው በማህበራዊ ተስትፎው ይቀጥላል ባህሪው ይገለጻል። ሰውበቤተስብ፣ በባል፣

TZTA: Page 11: October 23, 2012 ww.tzta.ca


TZTA: Page 12: October 23, 2012 ww.tztaca ከገጽ 6 የዞረ ደሞም መሆንም አለበት፣ እነዛ በኔ ላይ የሚጽፉት የነበሩት ፊቴንም አዙሬባቸው አላውቅም። በእውነቱ እግዚአብሄር በሚያውቀው ከውስጤ ምንም የሚሰማኝ ነገር የለም። እንዲሁ ስንል፤ በ2010 ላይ ይሄን ነገር መጀመር አለብን አልን። ቅድም እንደተናገርኩት ብዙ ሰዎች ቢያንስ አንድ ሚሊየን መያዝ አለባችሁ፣ የሚገርመው ነገር በጣም የእግዚያሔር ፈቃድ መሆኑ የሚታወቀው ኮንትራክተሮቹ የሶስት ሚሊዮን ተኩል ስራ ለመስራት ስንፈራረም ከባንክ ግማሽ ሚሊየን እንክዋን እንደሌለን ያውቁ ነበር። ባንክ ሄደን ስንጠይቃቸው እንዴ ምን አይነት ኮንትራክተር ነው ገንዘብ ሳይኖራችሁ እንዴት ተፈራረማችሁ ነው ያሉት። ገንዝብ ሳይኖር በሂድት ከሶስት ሚሊዩን በላይ ለኮንትራክተሩ ስንከፍል ባንኩ አንድ ሚሊየን ሊሰጠን ቃል ገባ። እንግዲህ ከባንክ የተበደርነው በፊት የነበረንና በኋላ የተበደርነው አንድ ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ ተበድረናል። እንግዲህ ይሄ ከስድስት ሚሊዮን ነጥብ አንድ ስታወዳድረው ወደ አምስት ሚሊየን የተጠጋሁት እኛው ሰብስበን ነው። ከሰማይ አልመጣም። ይህንን ስል በርግጥ አብቅቶአል ማለት አይደለም፣ እንግዲህ ይሄ በጥሬ ገንዘብ ነው እንጂ በጉልበት የተሰራው የተተመነው ወደ አምስት መቶ ሽህ ሲሆን ከእዚያ ጋራ ሲደመር ስድስት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ነው የሚሆነው። ያ ጽንሰ ሐሳብ አድጎ ይሄደውና እዚህ ደርሶአል። መጀመሪያ ደረጃ የዛሬ አስራ አምስት አመት ነው ይሄን አሁን ያለንበትን ገዝተን ስንገባ ነው ጽንሰ አሳቡ የነበረው እንጂ በዚህ በዌር ሃውሱ እንቀጥላለን የሚል አሳቡም አልነበረኝም። ይሄን ዌር ሃውሱን ጠጋግነን ከላይ መስቀል አድርገን እንዲያው አይምሮዬ አይቀበለውም ነበር። የኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ክጥንት ጀምሮ ስር መሰረት ያለው፣ ባህል ያለው፣ ስርአት ያለው ቤተክርስትያን ስለሆነ ልክ እንድዚያ አይነት ቤተክርስትያን እንዲሰራ ነበር ምኞቴና ድሪሜ እግዚአብሄር ሕያው አምላክ እውን አድርጎታል እግዚአብሔር ይመስገን።

ትዝታ፦ ህንጻው ምን ያህል ምእመናን ይይዛል? ምን ያህልስ የመኪና መቆሚያ ይኖረዋል? እንዲያው ስለሕንጻው ባጭሩ ቢገልጹልኝ?

አዲሱ ቤተ ክርስትያን ሕንፃ ሊቀካህናት፦ ሕንጻው እንግዲህ ሶስት ደረጃ አለው የመጀመሪያው ሰሙ ቤዝመንት የሚባለው በዚህ አገር ምድር ቤት የሚባለው ስፊ አዳራሽ አለው። በውስጡ ቢሮዎች፣ ወጥቤት፣ መሰባሰቢያ አዳራሽ፣ የሕጻናት ማስጠመቂያ አለው እንግዲህ ይሄ የመጀመሪያው ነው። ሁለተኛው ጠቅላላ ቤተ መቅደሱ ነው። በውስጠ የመጀመሪያው ፍሎር ስድስት መቶ ሰው የሚይዝ ነው። በወንበር ደረጃ የላይኛው ሶስተኛው ፍሎር የመጀመሪያው ፍሎር ስድስት መቶ ሰው ከመያዙ ጋራ እናቶች ልጆቻቸውን የሚያጠቡበት በዚህ አገር አባባል ኬር ሩም የሚባል አለ። እንደገና የአስተዳዳሪውና የጸሐፊው ቢሮ አለ። ከዛ ቀጥሎ ሁለተኛው ፍሎር ላይ እንደዚሁ የሰበካ ጉባዔው እና የሊቀ ጳጳሱ ቢሮ አለ። እንደዚሁም ደግሞ እንግዳ ቅዱስ ፓትሪያሪኩ የሚያርፉበት ለሳቸው የተዘጋጀ ሁሉን ነገር ያካተተ አለ ከፍል አለው። ከዚያ ቀጥሎ ደግሞ እስከ ሁለት መቶ ሃምሳ የሚይዝ መቀመጫ አለው። በእግር መውጫና መውረጃ ደረጃ አለው። ሁለተኛ ኢሊቨተር አለ። የቤተክርስትያኑ በር የመጀመሪያው ፊት ለፊት ሶስት ታላላቅ በር አለው። ከዚያ ቀጥሎ እንደዚህ አገር ሁኔታ ሁለተኛ በር ብርድ እንዳያስገባ የሚከልል አለው። ከመቀመጫው በፊት ሶስተኛ ደግሞ ሳይድ ዶር ሁዊል ቸር የሚገባበት አለው። ከዚያ ቀጥሎ በውንዱም በሴቱም መግቢያ በር ጫማ የሚያስቀምጡበት ክፍል አለው፣ ምክንያቱም ጫማ ተይዞ ስለማይገባ ለዛ ተብሎ የተዘጋጀ ቦታ አለ። ከኢሊቬተሩ ቀጥሎ የሴቱም የወንዱም መግቢያ ላይ ማስቀመጫ አለው። እንግዲህ ከቤተክርስቲያኑ በላይ አምስት ዶም አለው አንዱ የመካከለኛው ዶም በጣም ትልቅ ነው። በውስጡ ስእል ተስሎበታል። ሰእሉም የጌታችን የመዳሃኒታችን የየሱስ ክርስቶስ እርገቱን የሚያሳይ በዚያ በደብረዘይት እርሱ እየታየ ከሐዋሪያት ተለይቶ ያረገበትን የሚያሳይ፣ ሃዋሪያትም አንጋጠው እያዩ ያሳያል፣ እንደገና በሌላ በኩል ደግሞ ጌታችን መደሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ አለም እንደገና ለመጨረሻ ለህዝብ እንደስራው ለመክፈል በሚመጣበት ጊዜ በግራና በቀኝ አስራ ሁለቱን ሃዋርያት አስከትሎ ሃይላፋት መላይክት ከጀርባው ሆኖ ሲመጣ የሚያሳይ ስእል አለው። ከዚያ ፍለፊቱ የመግቢያው የመቅደሱ ሶስት በር አለው።፣ ከዚያ እንደገና በግራና በቀኝ ሁለት አለው በአጠቃላይ አምስት በር አለው፣ የመቅደሱ መግቢያ መንበሩ ከኢትዮጵያ መጥቶ የተሰራ ነው ሶስት መንበር አለው አንዱ ትልቅ በጣም ትልቅ መንበር ሁለቱ መጠነኛ የሆኑ በግራና በቀኝ የካሕናት መልበሻና ቤተልሔም አለው፣ የሚዘጋጅበት ከዚያ በኩል በግራና በቀኝ አልባሳት ማስቀመጫና አንዳንድ መጽሀፍ ማስቀመጫ አለው፣ አንዳንድ አባቶችም ሲመጡ ማንበቢያ ከፍል አለው። እንግዲህ ይሄን ይመስላል ከሞላጎደል በተክርስቲያኑ። እንግዲህ ፓርኪንግ በአጠቃላይ ዘጠና ስድስት መኪና ፓርክ የሚያደርግ አለን። በመሃንዲሱ የተሰጠን ማለት ነው እርግጥ በከተማው ፈቃድ መሰረት አንድ መቶ ሰላሳ መቆሚያ እንድናዘጋጅ ነው የተነገርን የሆነ ሆኖ ከጎረቤታችን ደግሞ በስምምነት በደብዳቤ የሰጡን ሃያ ስድስት መኪና ማቆሚያ አለው፣ ከዚያ ጋራ ሲደመር ወደ መቶ ሀያ ይሆናል ማለት ነው። ቅድም ካልኩት ጋራ ማለት ነው። አሁን ደግሞ በቅርቡ የታይኮስ መንገድ እስካሁን መንገዱ ላይ ማቆም አልተፈቀደም ነበር ነግር ግን አሁን

በሲቲው ህግ ሆኖ ወጥቷል። መኪና በዚያም እናቆማለን ማለት ነው። መኪና ማቆምያ ችግር ያለ አይመስለኝም። እርግጥ እስካሁን ድረስ ሲቲው በጠየቀው መሰረት ዲማንድ እያረገን ነው፤ እኛም ይሄንን ከጥናት ውስጥ አስገብተን አቅርበናል። አሁን ያሉን ጎረቤቶቻችን በደብዳቤ ብቻ ሳይሆን በጠበቃ የተደገፈ በማለት ጠይቀውናል፣ እንደሱ እናደርጋለን ምክንያቱም ለነሱም ጥቅም ስለሆነ እንሱ ብዙም መኪና በስራ ቀን ስለሆን እነሱም እኛጋ በስራው ቀናን ስለሚያቆሙ በዚህ ነው ስምምነቱ። የፓርኪንግ ችግር የለብንም። ትዝታ፦ ጠቅለል አድርገው ምን ያህል ሰው ይይዛል ብለው ያስባሉ ? ሊቀካህናት፦ በአጠቃላይ አክቲቭ የሆነ ምእመናን ያለን እስከ አምስት መቶ ነው እንደሚታየው በመዝገብ ላይ ግን ከአንድ ሽህ በላይ ነው ያለን። ትዝታ፦ ይህ ምን ማለት ነው ? ሊቀካህናት፦ እንግዲህ ይመዘገብና አይመጣም፣ ግን መዝገቡ ይኖራል አባል ነኝ ብሎ መጀመሪያ ይመዘገብና ይቀራል. አንድ አዳንዱ በስድስት ወሩ ይመጣል፣ አንድአንዴም በሶስት ወሩ። እኛ በሙሉ አባልነት የያዝናቸው አምስት መቶ ናቸው። በአጠቃላይ ቋሚ አባል አልን የምንለው እስከ አምስት መቶ ነው፣ ቅድም ተናግሬአለሁ በወንበር ደረጃ እስከ አንድ ሺ ይይዛል። ትዝታ፦መቼም ይህን የሚያህል ህንጻ ሲሰራ ከላይ ገልጸውልኛ ለማጠናከር ወጭውስ እንዴት ነው? ሊቀካህናት፦ ካሰብነው በላይ ነው ወጭው፣ ቀደም ብዬ እንደተናገርኩት አራት ሚሊየን ተኩል የፈጃል ነበር የተባለው በግርድፉ እስካሁን ድረስ የውጣው ግን ስድስት ነጥብ ሚልዮን አንድ መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ነው። ይሄ እንግዲህ በእቅድ ተይዞ ውጭ የሆነውን ነው። በጉልበት፣ በፈቃደኝነት የተሰራውን ካልኩሌት ስናደርገው መሃንዲሶቹ እንደነገሩን ከአምስት መቶ ሺህ በላይ ነው። እንዚህን የበጎ ፈቃደኝነት ስራ ስናከፋፍለው አንደኛ የኔ ብጤው የሚቆፍር፣ ድንጋይ የሚያቀብል፣ ብርት የሚያነሳ፣ የሚጠርገው፣ ምን የሚለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ሙያ ያላቸው በኮንስትራክሽን ሙያ ተቀጥረው የሚሰሩ ነገር ግን በትርፍ ጊዜአቸው መተው የሚሰሩ ሙያ ያላቸው ሰዎች፣ ሶስተኛ እንጂነሮች ኤለክትሪሽያኖች፣ መሃንዲሶች ላይሰንስ ያላቸው በብዛት አሉ ሰአሊዎች ካርፔንተሮች የመሳሰሉትን ያቅፋል። ትዝታ፦ እነዚህ ሁሉ የነጻ አገልግሎ የሚሰጡ ናቸው? ሊቀካህናት፦ አዎ! ለምሳሌ ያንን የመሰለ በዶም ውስጥ ስእል ስሎ አስር ሺህ ብር ሃያ ሺህ ብር ተከፈለ ማለት እንደኔ ምንም ማለት አይደልም፣ በጣም በጣም ድንቅ ነው! ለአንደኛው በተለይ ብዙ አገልግሎት ሰጥቶ የትራንስፖርቴሽን ያህል እንዃን አንከፍለውም። በነጻ እንደማለት ነው። እዚያ ውስጥ የተከፈለ ቢኖር የመንበሩ ስራና ደግሞ እግድግዳው ላይ ያለ የእንጨት ስራ፣ ውጪ ቅርሶች አሉ ምንም እንክዋን እንደሙያው እንደስራው ባይከፈለውም ከፍለነዋል። የበተቀረው በሙሉ እንጂነሮች ኤሌክትርሽያኖች መሓንዲሶች ላይሰንሲድ የሆኑ ናቸው ደግሞ እንዚህ በነጻነው እየሰሩ ያሉት! ትዝታ፦ እንዲያ በግምት ስንት ይሆናል ብለው ያስባሉ? ሊቀካህናት፦ እንግዲህ በጠቅላላው እንጅኔሩ ሁሉንም እንደገመተልን ከአምስት መቶ እስከ አምስት መቶ ሰባ ሺህ ይሆናል፣ ግን ከዛ በላይ ነው ስናየው፣ ይሄ እንግዲህ ስእሉን፣ የመንበሩንና፣ የአርት ስራውን አይጨምርም። መሃንዲሱ ባወጣው ብቻ ነው። ስእሉን ሲያይ ደንገጠ! መሃንዲሱ ማለትነው፣ በጣም ነው የሚደነቀው! አንደኛ እንዴት አድርጎ ነው፣ ሁለተኛ እርቀቱ ወደላይ በጣም እሩቅ ነው በመሰላልም የሚደረስ አይደልም። ዶሙን ሲያስቀምጡ ያደርጉት ፕላት ፎርም ልዩ መሰላል አስቀምጠው ነው። ከዚያ በላይ ወደ ላይ ወደ ሰላሳ አምስት ሜትር ነው እርቀቱ እዚያው ላይ ነው ስእሉ የተሰራው እጅግ በጣም በጣም ድንቅ ነው!! ዋጋ እንኳን ቢከፈል ተከፈላቸው አይባልም፣ ስራው ድንቅ ነው! ሌላው እንግዲህ ገንዘቡን ካልኩሌት አርገን ስናስቀምጠው አንድ ነጥብ ስድስት እንዲያውም ስድስት ነጠብ ስድስት እንበለው እንጂ በጠቅላላው ዙሪያውን ያየነው እንደሆነ ከዚያ በላይ ነው። ሁለተኛ ደግሞ ያለብን እዳ የተበደርነው ባሁኑ ሰአት አንድ ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ ነው። ሁለት መቶ ሺህ ድሮ ሲጓተት የቆየ፣ መጀመሪያ ሁለቱን ሕንጻ ስንሰራ የተበደርነውና አዳራሹን ያሰራንበት ስለነበር ሁለት መቶ ሺህ ነበር ከዛ ጋራ ሁኖ አንድ ሚሊየን ሰባት መቶ ሺህ አለብን። አንድ ሚልዮን ሰባት መቶ ሺህ ከዛኛው ጋር ሲወዳደር ለኛ ብዙ አያስጨንቀንም። የቶሮንቶ ሕዝብ በእውነቱ የሚደነቅና የሚያስገርም ሕዝብ ነው። ይህንን በትንሽ ጊዜ የከፍለዋል ብዬ አምናለሁ። እንዲያው ምንም ጥርጣሬ የለኝም ይህን ሁሉ የከፈለ ሕዝብ ይህችን ለመክፈል እዳነው ብሎ አይዘውም ነው የምለው። ትዝታ፦ ስለ ገዘብ ነክ ለምዕመናኑ የሚሉት ካለ? ሊቀ ካ ህ ና ት ለምእመናኑ የምለው በመጀመሪያ አሁንም ስራችሁን ይባርከ፣ የሰጣችሁት የደከማችሁበት ህያው ሆኖ ለዚህ

ድርሰናልና በጣም ደስ ይበላችሁ ነው የምለው። ይሄ ያንድ ሰው የሁለት ሰው ሳይሆን የጠቅላላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ምእመናን ስራ ስለሆነ ሁላችሁንም እግዚአብሔር ይባርክ ነው የምለው። ከፍ ብዬ እንደተናገርኩት ለዚህ ስራ፣ ለዚህ ድንቅ ስራ የሚመሰገነው ባለቤቱ እግዚአብሔር ነው፣ በለቤቱን መጀመሪያ እሱን መነሻ አድርገን ስለተነሳን እሱ ጩኽታችንን ሰምቶአል፣ የመነሻችን ቃላት የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፣ እኛ ባሮቹ ተነስተን እንሰራለን፣ እኛ መሳሪያ ነው የሆነው፣ የሰራው እሱነው እሱ ነው። በበለጠ መመስገን ያለበት ፈጣሪያችን አምላካችን እና ይኽን ሁሉ ስራ ስንሰራ አንደኛ የመከረ፣ ያዋኽደ እሱ ነው። ባለቤቱ ለምእመናኑ አሁን የማሳስበው አሁን ከላይ የጠቀስዃት ገንዘብ አለች። ይህንን ለመክፈል ውደዃላ እደማትሉ አምናለሁ። ሌላው አሁን ወቶአል ካልኩት ሌላ ያልተሰራ ስራ አለ። ፓርኪንጉ አትክልቱ የሚሰራ ስራ አለ እሱም ሌላ ተጨማሪ ወጪ ነው፣ ይሄን ያህልም ባይሆን አሁንም ወጪ ይኖራል ማለት ነው። ምናልባት በአመት ውስጥ ሁሉንም እናጠቃልላልን ብዬ አስባለሁ። በአመት ፓርኪንጉን፣ አትክልቱን ዙርያውን ያልቃል ብዬ አምናለሁ። አሁን ለምረቃው በአል ዙሪያውን ይደለደላል አሸዋ ይደረጋል። አሁን የድሮው ስማኒያ አራት ታይኮስ ፈርሶ ተደልድሏል በአፈር የቀረው ደርጃውን ስርተን በአሸዋ መደልደል ነው ለጊዜው ይህም አሁን እየተሰራ ነው ያለው። ትዝታ፦ አሁን ኖቨምበር 17 ቀን 2012 ዓ.ም. ኖቬምበር 18 ቀን 2012 ዓ.ም. ቤተክርስቲያኑ ይመረቃል። ስለዚህ ለሕዝቡ የሚሉት ካለ? ምንያህል እንግዶች ይመጣሉ? ከየት? እነማን? ሊቀካህናት {አዎ እንግዲህ ይሄ በፈረንጆቹ ኖቬበር አስራ ስባትና አስራ ስምንት ሁለት ሺህ አስራ ሁለት ሲሆን በኢትዮጵያ አቆጣጠር ደግሞ ህዳር ስምንትና ዘጠኝ ሁለት ሺህ አምስት መሆኑ ነው። ያን ግዜ ይባረካል ብልን እንገምታለን። ቅዳሜና እሁድ መሆኑ ነው፣ ይህንን ስራ እንግዲህ ያቀድነው። ቀደም ብሎ እንደመሃንዲሶቹ ሃሳብ በሃምሌ ላይ ነበር የታሰበው ያ ሳይሆን ሲቀር ውደዚህ አዛውረናል። በአሁኑ ሰአት ግን ብዙው ነገር እየተጠናቀቀ ነው። ይህንንም የምለው እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንዲሆን ነው። እስካሁን ድረስ በስኬጅዋሉ መሰረት ሁሉ ነገር እየተጠናቀቀ ነው ያለው ግን ነገ የሚሆነውን አናውቅም። ሁሉ ነገር ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር ነው፣ በኛ እቅድ መሰረት እስካሁ ሰአት ድረስ በእቅዳችን መሰረት ስራው እየተጠናቀቀ ነው ያለው። አሁን ውስጡ ተጠናቋል ምንም የቀረ ነገር አለ የምለው ነገር የለም። ውስጡ ውጭው ደረጃውና መንግስት የሚፈቅድልን ውሃ አለ እሱን ተፈቅዷል ግን ገና አልገባም፣ የመብራቱ ሃይድሮ አልቋል፣ ትርንስፎርመር ይገባል ብለዋል እሱን እየጠበቅን ነው ይቆማል እያሉን ነው፣ በዚህ መሰረት ሁሉ ነገ እየተካሄደ ነው ያለው ለዚያ እግዚአብሔር ከፈቀደ ለዚያ ቀን ከፈቀደ። ምእመናኑን በዚህ አጋጣሚ የምነግረው አንደኛ ሰዎች እንዲጋብዙ ለማስተናገድ ሁለተኛ ይህን የመሰለ ድንቅ ስራ ለቤተክርስትያንዋ ብዙ ነገር ያስፈልጋልና ያን ጊዜ እያንዳንዱ በተለይ የቶሮንቶ ምእመናን አስተናጋጅ እንጂ እንግዳ ብቻ እንዳይሆን አሳስባለሁ። ምክንያቱም ከኢትዮጵያም የሚመጡ አሉ ለምሳሌ በሃምሌ ወር ሰዎች መጥተው ነበር ለዚሁ በአል ብለው አሁንም የሚመጡ አሉ። ከኢሮፓም የሚመጡ አሉ፣ ከአሜሪካም የሚመጡ አሉ። ቅዱስ ፓትሪያሪኩ ይመጣሉ። ሌሎች ጳጳሳት ከየቦታ የሚመጡ አሉ እና ስለዚህ የቶሮንቶን ምእመናን የምጠይቀው ይህንን ድንቅ ስራ የሰራችሁ ሁሉ አሁንም ለዚያ ለበአሉ እለት ተገኝታችሁ ተስተናጋጅ ሳትሆኑ አስተናጋጆች እንድትሆኑ ነው የምጋብዘው እግዚአብሔር አምላክ ለዚያ ያብቃን። ትዝታ፦ ከርጅም ጉዞ በኋላ ለዚህ በቅተዋል ከዚህ የሚቀጥለውስ? ሊቀካህንት፦ እንግዲህ እግዚአብሔር እንደፈቀደ ነው መቸም ወደፊት ለልጆች ትምህርትና ስኔር ሆም ለማሰረት ነው። ይሄ መቸም ሰው ያስባል እግዚአብሔር ይፈጽማል ነው። እኛ እንግዲህ ወጣት እንደሆንን አልቀረንም ይሄው እንግዲህ እንደምታየኝ የዛሬ ስላሳ አመት ስመጣ ጎረምሳ ወጣት ነበርኩ አሁን እንግዲህ ጥቁር ጸጉር የለኝም ሁሉም ነጭ ሆኖአል። ከእንግዲህ ወዲያ የማርጀት ሁኔታ ነው። ይሄ የተፈጠሮ ህግ ነው። በጠቅላላው ከመቶ ዘጠና ፕርሰንቱ ከኔ እድሜ ጀምሮ በታች ያለነው ከኔ በላይ የሉ ቢኖሩ በጣም ጥቂቶች ናቸው። አሁን እንግዲህ በአንድ ዘመን ነው ጡረታም የምንወጣው ማለት ነው። አብዛኛው ህዝብ ማለት ነው አንድላይ ሆነን እግዚአብሔርን እንድናመሰግን በእርጅና ዘመናችን በአንድ አካባቢ እንድንሆን እግዚአብሔር እንዲረዳን የሽማግሌዎች መኖሪያቤት ለማሰራት እቅድ አለኝ እንዲያውም ይህንን ካስመረቅሁ በሁዋላና ሁሉ ነርገር ከተዘጋጀ በሁዋላ ይሄንን እንዳከናውን እግዚብሔርን እጠይቀዋልሁ እቅዴ እንደዚያ ነው። ትዝታ፦ ይህ ቤተክርስትያን ከምረቃው በኋላ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል ለሴቶች ለወንዶች ለወጣቶች ለልጆች የሚያስተላልፉት መልክት ካለ? ሊቀካህናት፦ አዎ እንግዲህ እኔ እውነትን ነው ይምናገረው የዛሬ ሃያ ስምንት አመት ሰው አልሰባስብልኝ ብሎ በነበረበት ጊዜ ቢጨንቀኝ ሌሎቹን አባተ ክርስትያናት ካህናትና ጳጳሳት አነጋግሬ ነበረ። እንዴት ነው ሁሉም እንደምታውቀው የካናዳ ህዝብ ከውጪ የመጣ ነው። ነጭ ብትለ ጥቁር ብትለው ሁሉም እሚግራት ነው እና እሚግራት ሆኖ መጥቶ ከሁለተኛው አለም ጦርነት ወዲህ እራሱን ችሎ ትልቅ ት/ቤት ዩኒቨርስቲ ተቋማትን አሰርቶ ይኖራል። እነሱን አነጋገርኩኝ በተለይ የግሪኩ ሊቀ ጳጳስ ሕዝቡ አልመጣልኛ አለ በሬዲዮ ተናገርኩ፣ በጋዜጣ አወጣሁ፣ በቴሌቪዥን ሳቀር በሁለቱም ቋንቋ ጥሪ

አደረኩ ምዕመናኑ አልመጣም ብዬ ስጠይቀው ግድ የለሕም ይመጣም አይምጣም አንተ ግን ከቦታው እንዳትለይ ብሎ መከረኝ። አንድ ነገር አስጠነቀቀኝ! ያስጠነቀቀኝ ምንድነው ቤተክርስቲያኑ ይቀጥላል፣ ስታስተምር ግን በራስህ ቋንቋ ብቻ እንዳታስተምር። የመጀመሪያውን ትውልድ ታጠዋለህ። በእንግሊዝኛም ጭምር አስተምር፣ ውጣቱን እዚህ የሚወለደውን ለመያዝ ይህን ማድረግ አለብህ። እኛ ግሪኮች የመጀመሪያ ትውልድ አምልጦናል። እንዲያውም አብዛኛው ፕሮቴስታንት ሆኖአል ምክንያቱም አርቶዶክስ ነን። እኛ ከኦርቶዶክስ እየወጣ የዚህን አገር ባህል ይዞ ጥሎ ሄዶአል። ስለዚህ ለመያዝ በሁለቱ ቋንቋዎች እንድታስተምር ብሎኝ ነበር። አሁን ጊዜው ይመስለኛል እስካሁን ብዙም አላደረግነውም። ወጣቶች አሉን፣ እንግሊዝኛም የሚናገሩ አሉን፣ ተነጋግረናል እንዲያውም ቅዳሴ ውደፊት ሁለት ጊዜ እንቀድሳለን፣ ሶስት መንበር ስላለን በአንዱ መንበር ጠዋት ቀድሰን እንደሆነ በአንደኛው መንበር ደሞ በተለያየ ሰአት እንቀድሳለን። እቅድ እያወጣን እያመቻቸን ነው ያለነው። ይህን በቅርብ ጊዜ እናደርጋለን ምክንያቱም ይህን ወጣቱን ትውልድ ለመያዝ በቋንቋው ማስተማር አለብን እንሱ ደግሞ ለዚህ ተሳታፊ እንዲሆኑ እንጠይቃለን የሚቀጥለው ይሄው ነው እቅዳችን። ት ዝታ፦ ይሄ እንክዋን ለየት ያለ ነው ስለትዝታ ጋዜጣ ያለዎትን አስተያየት ቢሰጡኝ? ሊቀካህናት፦ ትዝታ ጋዜጣ በዚህ በቶሮንቶ ለረዥም ጊዜ ያገለገለ በመሆኑ በጣም አደንቃለሁ። ብዙ ጊዜ ኢትዮጵያውያኖች ጋዜጣ ያሳትማሉ ይጀምራሉ መጽሔት ይጀምራሉ ያሳትማሉ ከዛ በኋላ ይተውታል። ለብዙ አመታት አንዱ በቶሮንቶ መገናኛ ዘዴ የሆነው የትዝታ ጋዜጣ ነው። ለቤተክርስትያናችን ደግሞ ትዝታ ብዙ አስተዋጽዎ አድርጎአል ምክንያቱም ሰው መቼም ኢንፎርሜሽን ካልተለዋወጠ እውቀት ሊኖረው አይችልም፣ ለቤተክርስትያናችን ለኮሚኒቲያችን ብዙ አስተወጽዎ እያደርገች የምትገኝ ጋዜጣ ነች፣ በጣም ነው የማደንቀው! እንኳን ደስ ያለህ ነው የምለው። እንደዚህ ያለማቋረጥ የሚቀጠል አይወድቅም የሚወድቀው በራሱ ነው እና በጣም በጣም ነው የምደሰተው ሁል ጊዜ። ትዝታ፦ ከላይ ያልጠየክዎት፣ የሚሉት ነገር ካለ? ሊቀካህናት፦ እንግዲህ በአሳቤ አሁንም ላመሰግን የምፈልገው ለዚህ ደረጃ ያበቃንን አምላኬን ነው። የለመኑትን የማይነሳ የነገሩትን የማረሳ አምላክ ነው እና ስራ ስንጀመር አቀበትና ቁልቁለት እንዳለው መውደቅ መነሳት እንዳለው ማንኛውም ሰው ማመንና መረዳት አለበት። ሁልጊዜ ሁሉ ነገር ገና መንፈሳዊ ስራ ነው ገና ለኮሚኒቲ ነው የምሰራ ብሎ ሁሉ ነገር አልጋ ባልጋ ይሆናል ሁሉም ይደግፈናል ብሎ ማሰብ ልክ አይደለም ብዬ መናገር እወዳለሁ። ብዙውን ጊዜ የምንወድው እኔ የምሰራው ለህዝብ ነው፤ እንዴት ይቃወመኛል የሚለውን በእውነቱ ከአይምሮአችን እንዲወጣ ያስፈልጋል። አንደኛ ያለንበት አገር ይህንን ያስተምራል፣ ሰው በተፈጥሮ የተለያየ ሀሳብ ነው ያለው የተለያየ አሳብ ሲኖረው ከራሱ ሃሳብ ውጭ የሆነው መልካም ቢሆንም የመቃዎም ተግባር አለው፣ ስለዚህ ያንን እንደመጥፎ ነገር ቆጥሮ የያዝኩት ለካ ትክክል አይደለም ብሎ እንዳይተው በዚህ አጋጣሚ ማሳሰቢያ እሰጣለሁ። ለኢትዮጵያውያን በሙሉ የጀመርነውን እስከ መጨርሻው ድረስ ይዘን መገዝ እንዳለብን ነው ማሳሰብ የምወደው። አሁንም ሌላ ስራ ይኖራል ያለነው በስደት ነው ያለነው በሰው አገር ነው። ባለንበት ግን ስራ መስራት እንችላለን ይህንን ካልኩ በኋላ ወደ አገሬ እመለሳለሁ በአሁኑ ሰአት ኢትዮጵያ ላይ አንድ የተከሰተ አለ ሕዝብ ሊገነዘበው ይገባል ባንድ ወቅት ባንድ ወር ሁለት መሪዎች አርፈዋል። አገር እንመራለን የሚሉ ቤተክርስትያን እንመራለን የሚሉ ከሰማኒያ ሚሊየን በላይ ሕዝብ እንመራለን የሚሉ ነበሩ፣ ከአርባ ምሊየን በላይ የኦርቶዶክስ ተከታይ እንመራለን የሚሉ አልፈዋል ምናልባት ሰዎች የተፈጥሮ ህግ ነው ሊሉ ይችላሉ ግን እኔ ትልቅ መልክት እግዚአብሔር አሳይትዋል፣ ስለዚህ የሞቱትን ነብሳቸውን ይማር ብለን እኛስ በህይወት ያለነው ምንድነው የምናደርገው ብለን ማሰብ እንዳለብን አሳስባለሁ። በአጭር ጊዜ፣ ባልታሰበ ሰአት ውስጥ እንደምንሄድ እያንዳዳችን ማወቅ ይኖርብናል። መልካም ስራ ሰርተን ለትውልድ የሚጠቅም ስራ ሰርተን በዛች በተስጠችን አጭር ጊዜ ውስጥ ጥሩ ስራ እንድንሰራ አሁን ዛሬ ባገራችን ውስጥ ሁለት እራስ እንዳለ አቃለሁ። ግማሸ በሞቱ የሚደሰት ግማሹ በሞቱ የሚያዝን የተፈጥሮ ህግ ነው ግማሹ ሲያለቅስ ግማሹ ይስቃል ግን እንደሰው እንደ ኢትዮጵያዊ ግን ከዛ ባሻገር ማሰብ እንዳለብን ነው በማለት አሳስባለሁ። በዚህ አጋጣሚ በመደሰትና በማዘን ብቻ አይደለም ከዛ ባሻገር ማየት መቻል አለብን ምንድነው፣ ለአገራችን እንዲሆን የምንፈልገው ምንድ ነው? ለቤትክርስትያናችን እንዲሆን የምንፈልገው የተከፋፈለች አገር የተከፋፈለች ቤተክርስትያን ለትውልድ ልናስረክብ ነው? ወይንስ አንድነት ያላት ሀይል ያላት ፍቅር ያላት አገር ትክክልኛ የክርስቶስን ወንጌል የምትሰብክ አንድነት ያላት ቤተክርስትያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ተዘጋጅተናል? ያንን እንድናደርግ እግዚአብሐር ምልክት አሳይቶአል። ይህንን ምልክት ሁሉም እንዲገነዘብ ያስፈልጋል። ይሄ ጫፍና ጫፉ ማልቀስና ማዘኑ ለሚቀጠለው ትውልድ ፋይዳ የለውም። እንዚያ አልፈዋል አሁን እኛ ተርክበናል የሚል ትውልድ ያስፈልጋል። ለዚህ የማሳስበው የተለያየው ወደ አንድነት የተጣላ ወደእርቅ እንዲመጣ በራሴ እንደ ኢትዮጵያዊነቴ በጣም አሳስባለሁ። ሁል ጊዜ የሚያሳስበኝ ስለሆነ እግዚአብሔር አምላክ ይህንን የተናገርኩትን ሁሉ በሌላ ትርጓሜ እንዳትተረጉሙ እያሳሰብኩ በዚህ እሰናበታለሁ አመሰግናለሁ። ትዝታ፦ እኔም ለሰጡኝ ቃለ መጠይቅ አምሰግናለሁ። እግዚአብሄር ይስጥልኝ።


TZTA: Page 13 : September 18, 2012: www.tzta.ca

ቤት መሸጥ ወይም መግዛት ይፈልጋሉ? 2011

Samuel Bekele Presidential Award Winner 2011

* አስፈላጊውን ምክር እሰጣለሁ። * የሚፈልጉትን አካባቢ በተመለከተ ለሥራዎ ሆነ ለቤተሰብዎ የሚስማማ ቦታ እንዲያገኙ ምክሬን አካፍልዎትለሁ። * በቀላሉ ሞርጌጅ (በአነስተኛ ወለድ ለቤትዎ መግዣ) ለማግኘት ሁንታዎችን አመቻቻለሁ። * በሁኑ ጊዜ ባለው ዝቅተኛ (Interest Rate) ተጠቅመው የቤት ባለቤት ለመሆን ከፈልጉ በቀጥታ ደውለው ሊያነጋግሩኝ ይችላሉ።

ደውሉልኝ። ሳሙዔል፦ ደውሉልኝ። Cell:-ሳሙዔል 416-996-3729 በቀለ Bus.: 416-391-3232

416-996-3728

Samuel Bekele Sales Representative Bus: 416-391-3232 Cell: 416-996-3729 Fax: 416-391-0319

ሥራ መጀመራችንን በደስታ እየገለጽን፣ የታክስ መስሪያው ጊዜ ሳያልቅ ይጎብኙን። ማግኘት የሚገባዎትን ገንዘብ እናስመልስልዎታለን።

ደውሉልን! ጎብኝን!


TZTA: Page 14: October 23, 2012: www.tzta.ca

THE PALACE

BANQUET HALL

(AHENFIE)

Affordable Banquet Hall for all occasions! Plenty Parking

We will provide you with all you needs for:

Wedding - Birthday - Parities - Anniversaries Meeting - Family Events - Puberty Ceremony - Banquet - Receptions & Engagements - & Much More... ለሠርግ፣ ለልደት፣ ለተለያዩ ስብሰባዎች፣ ለቀለበት፣ ለፓርቲ ና ለመሳሰሉት ሁሉ እናንተ በምትከፍሉት ዋጋ ተዘጋጅቶላችኋል። በተለይ ለመረዳት ጆርጅን ስልክ ደውላችሁ አነጋግሩ። ዋግችን ተመጣጣኝ ሲሆን በቅቂ የመኪና ማቆሚያም አለን።

For detail information call George Boadi @ Office:- 905-8515491 * Cell:- 416-709-8416 4120 Steeles Avenue West Suite 11 & 12 Woodbridge, Ontario, L4L 4V2 E-mail:- thepalace@gmail.com * www.the-palace.ca

ዘመን እንጀራ ZEMEN INJERA

2045 Danforth Ave. Danforth and Woodbine የሚገኘው መደብራችን የምንሸጠው እንጀራ ብቻ ሳይሆንቅመማ ቅመም፣ሽሮ፣ በርበሬ፣ እንጀራና የገብስና ይጤፍ ዱቄት፣ የጠላ እህል፣ ቡና፣ ኮሊንግ ካርድ፣ ሲዲ፣ ዲቪዲ እና የግሮሰሪ ሸቀጣ ሸቀጦችን ሌሎችንም ይዞ ይጠብቃችኋል። ድፎ ዳቦ እናዘጋጃለን። የእንጀራ ምጣድ እንሸጣለን። Zemen Injera proudly introduce you the opening of its store located at 2048 Danforth Avenue. We are not only sale Injera alone, we also sale all sort of grocery variety items like Spices, vedio, CD, DVD,Phone Cards & the like.

ይጎብኙን ወይም ይደውሉልን Tel: 647-887-4754 or 416-572-0447


TZTA: Page 15 : October 23, 2012: www.tzta.ca

ማስተር ኢቪት ጎንዳ * ሁለት ጊዜ በኦሎምፒክ የተካፈለች (በአቴንና በቤጂንግ) * አስራ አንድ ጊዜ ብሔራዊ ቻምፒዮን

ማስተር ቶሚ ቻንግ ማን ናቸው?

* በዓለም አቀፍ 7ኛ በቴክዋንዶ 7ኛ ዲግሪ ያላቸው አስተማሪ * በካናዳ የተክዋንዶ ምክትል ፕሬዘዳንት * ላለፉት ጊዚያት ለሚከተሉት በተግባራዊ ውጊያ አስተባብሪ . የኒከን ተከታታይ የቲቪ ፕሮግራምና አሁንም የቀጠለ . አዲስ ተጋባራዊ ውጊያ በፓስፊክ ሪም የፊልም ሥራ * በካናዳ የቴክዋንዶ ቲም ዋና ሥራ አስኪያጅ * በካናዳና ኮሪያ ማህበር ዋና ፀሃፊ * ሌላም ሌላም ከፍተኛ ሥራ እየሰሩ ይገኛሉ።

ማስተር ቻንግ ከብዙ ሆሊውድ አክተሮች ጋር አክሽን ፊልም ሠርተውል፡ አሁንም እየሰሩ ናቸው። ማስተር ሺን ዎክ ሊም ማን ናቸው?

* የካናዳ ብሔራዊ ቲም ኮች * 3 ጊዜ የብሔራዊ ቻምፒዮን * በ2008 የፔጂንግ ኦሎምፒክ ቲም ኮ * ክ2004 - 2012 በብርቲሽ ኮሎምቢያ የቴክዋንዶ ዋና ኮችና ሊቀመንበር * ከ1999 - 2005 የብሔራዊ ቲም ማህበርተኛ

ለምሳሌ ብንጠቅስ ጃኪ ቻን፣ ቪን ዲያዚል ስቴቨን ሲጋል ስማቸው ያልተጠቀሰ ሌሎችንም የሆሊውድ አክተሮች ያጠቃልላል።

ይህንን ማስታወቂያ ይዛችሁ ከመጣችሁ

20%

ከማንኛውም የተኮንዶ ፕሮግራም ቅናሽ ሲኖራችሁ፤ ነፃ ዩኒፎርም ታገኛላችሁ።


TZTA: Page 16 : October 23 , 2012: www.tzta.ca


TZTA: Page 17: October 23, 2012: www.tzta.ca

ከዚህም ከዚያም

ለግርድና የሚሄዱት እህቶቻችንን ልንደርስ የምንችልባቸው 4 መንገዶች – ገለታው ዘለቀ

በኣረብ ኣገራት ለግርድና የሚሄዱትን እህቶቻችንን የሚደርስባቸውን ስቃይ መናገር መነሻዬ ኣይደለም። ያልፍልኛል፣ እናት ኣባቴን እጦራለሁ እያሉ ወደ ሊባኖስና ሌሎች የኣረብ ገልፍ ኣገራት የሚጎርፉት እህቶቻችን ከሰባዊነት ደረጃ ዝቅ ብለው ሲሰቃዩ ሌላው በተለያየ የኣለም ክፍል ያለው ኢትዮጵያዊ ከንፈሩን ከመምጠጥ ያለፈ ብዙ ነገር ሲያደርግ ኣይታይም። እግዚኣብሄር ይባርካቸውና የተለያዩ ሰባዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች የቻሉትን ሁሉ እየታገሉ ነው። ግን ኢትዮጵያዊው የበኩሉን ለመወጣት ከማንም በላይ የሞራልም የዜግነትም የውዴታ ግዴታ ኣለበት። የዛሬው ጽሁፌ በሌላው ኣለም ያለው ኢትዮጵያዊ ምን ሊያደርግ ይችላል? በሚል ተግባራዊ ዘዴዎችን ለመጠቆም ነው። በመሆኑም ለእህቶቻችን በሚከተሉት መስመሮች ልንደርስላቸው እንችላላን። 1) ለወገን ለሃገር ተቆርቋሪ በሆኑ ኢትዮጵያዊያን የተቋቋመው ኢሳት ቴሌዚዥን ድርጅት በኣፋጣኝ መቀመጫውን ሊባኖስ ያደረገ የሪፖርተር ቡድን ሊልክ

ያስፈልጋል። ይህ ቡድን በየጊዜው የሚደርሰውን በደልና እንግልት እየዘገበ በማጋላጥ ችግራቸውን ሊቀንስ ይችላል። ኣንዱ ትልቁ ችግራቸውም በየሜዳው እየሞቱ ወደ ሚዲያ ስለማይወጣ ነው። ይህ ቡድን በየጊዜው በሚያደርገው ኢንቬስትጌቲቭ ሪፖርት ለኣለም ኣቀፉም ሆነ ለ ኢትዮጵያዊያን ያሳውቃል። ኣንዱ ችግር የኢንፎርሜሽንም ነው። ባለፈው እህታችን ኣለም ደቻሳ የሞተች ጊዜ ነው ትንሽ የተደናገጥነው። ያ ወደ ሚዲያ ስለወጣ እንጂ ሚዲያ ሳያውቃቸው የሚገደሉ የሚሰቃዩ ብዙ ናቸው። ባለፈው የ ሂውማን ራይት ዎች ባውጣው ዘገባ ላይ እንደሚያሳየው በየ ሳምንቱ ኣንድ የቤት ውስጥ ሰራተኛ ተፈጥሮኣዊ ባልሆነ መንገድ ይሞታል። እንግዲህ ልብ በሉ በሊባኖስ ውስጥ ወደ 200 ሺህ የሚጠጋ የቤት ውስጥ ሰራተኛ ያለ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ከ 60 እስከ 70 ሺህ የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ናቸው። ይህ ማለት በየ ወሩ ሁለት የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ወይ ተገለው፣ ወይ ታመው ፣ወይ የሚያሳክማቸው ኣጥተው፣ ወይ ራሳቸውን እንዲያጠፉ ተገደው ይሞታሉ ማለት ነው። ከዚህ የከፋ ነገር የለምና ኢሳት ባስቸኩዋይ ደርሶ ወገንተኛነቱን፣ ኢትዮጵያዊነቱን ማሳየት ኣለበት።

2) በ ኣሜሪካን ኣገር ኣዲስ የተቋቋመው የሴቶች መብት ድርጅት ኣስቸኳይ የቤት ስራው ሊሆን የሚገባው የህግ ባለሙያ የያዘ ኣንድ ቡድን መላክ ነው። በርግጠኝነት ለመብታቸው ለሚሟገት በደላቸውን ወደ ብርሃን ለሚያወጣ ድርጅት ወጪውን እንደሚሸፍኑ እምነቴ ጽኑ ነው። ከሚያገኙዋት ጥቂት ገንዘብ ላይ እያዋጡ ወጪውን ሊሸፍኑ ስለሚችሉ ድርጅቱ በባጀት በኩል ስጋት የሚገጥመው ኣይሆንም። የተጨነቁ እህቶች ኣለን የሚላቸው ካገኙ የሚከፈለውን መስዋእትነት ይከፍላሉ። እነዚህ እህቶች ከ ኤምባሲ ያጡትን የምክር ኣገልግሎትና ፍቅር ይህ ለመብታቸው የቆመ ድርጅት ይክስላቸዋል። 3) ለሲቪክ ማህበራትና ለ ፓለቲካ ድርጅቶች። ለግርድና የሄደችው እህታችን ስትሰቃይ ዛሬ ስትገደል ከንፈራችንን እየመጠጥን ችግሩ የሚፈታው የችግሩ ምንጭ የሆነው ኣምባገነን መንግስት ሲወገድ ነው ማለት ኣግባባ ኣይደለም። እሱን ማን ኣጣው? ኣሁን በመሃል ግን ድምጻቸው ታፍኖ ተዘልለው የሚያነቡትን እህቶች ኣይዙዋችሁ ማለት ግፋቸውን ማጋለጥ በርግጥ የህዝብ ፍቅር ያለው ድርጅርት ተግባር ነው ። የነሱን መከራና ግፍ ለፓለቲካ ፍጆታ መጠቀም ፈጽሞ ሊሆን ኣይገባም።

በመሆኑም ሁለቱም ኣይነት ድርጅቶች በመገናኛ ብዙሃኖቻቸው ይህን በደል ማውጣት ማሳየት ሰላማዊ ሰልፍ ማቀድ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። ሌላው ደሞ ለዚህ የዳረጋቸውን ኣስከፊ ስርኣት ለመለወጥ እንዲችሉ ሊያደራጁዋቸውም ይገባል። 4) ሌላው ከፖለቲካው ተገልሎ ያለው ኢትዮጵያዊ በሙሉ በያለበት ድምጹን በተለያየ መንገድ ማሰማት ኣለበት። በፌስ ቡክ በሰልፍ ወዘተ. ተቃውሞውን ማሰማት ኣለብት። ኣንዲት ኣረብ ኣገር የምትኖር እህታችን በስሜት ስትናገር እህቶቻቸውንና ሴቶቻቸውን ኣውጥተው ለግርድና የሰጡ ወንድሞች እንደ ኢትዮጵያዊያን ኣላየሁም ብላለች። ድሃ ኣገር እኛ ብቻ ኣይደለንም ግን እንደኛ ሴቶች ለግርድና ሄዶ የሚሰቃይ የለም ብላለች። በመሆኑም ኣለማቀፋዊ ተቃውሞ በማድረግ እህታችንን ልንደገፍ ይገባናል። እነዚህ ከፍ ሲል ያነሳሁዋቸው ነጥቦች በውነት በጣም ቀላል ልንሰራቸው የምንችላቸው ናቸው። እግዚኣብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!

መምህሩም ያስተምር ተማሪውም ይማር፤

የተማረ ሆኖ ዕውቀቱን የማይገልጽ፣ ባለፀጋ ሆኖ ገንዘቡን የማይሰጥ፣ ደሃ ሆኖ መሥራት የማይሻ ልቡ፣ ሶስቱም ፍሬ ቢሶች፣ ለማንም አይረቡ።’ ታዋቂው ደራሲ ከበደ ሚካኤል ይህንን ብለውን

አልፈዋል። ደራሲው ዕድሜ ለግሷቸው መምህሩም ለማስተማር ተማሪውም ለመማር አለመቻላቸውን ዛሬ ቢያዩ ምን ይሉ? በሃያ አንደኛው መቶ ዓመት ጉግ ማንጉጎች ተፈጥረው የዕውቀት ጮራ በሃገራችን ምድር እንዳይፈነጥቅ ጋርደዋት በጭለማ ውስጥ ትገኛለች። ‘እንዳያማህ ጥራው እንደይበላ ግፋው’ እንደሚባለው በአለፉት ሃያ ዓመታት ዩኒቭርሲቲዎች ተከፈቱ ቢባልም፤ የተማሪዎቹ ቁጥር ቢጨምርም፤ ተቋማቱ የመማርና የማስተማር ሥራ የሚካሄድባቸው ሥፍራዎች ሆነው አልተገኙም። የአካዳሚ ነፃነት በሌለበት በዕውቀት እድገት የለም። ተቋሞቹ የዕውቀት መገብያ ሳይሆኑ የካድሬ መፈልፈያ የስለላ ሥራ ማካሄጃ ናቸው። ይህም ሁኔታ በነፃነት መምህሩም ለማስተማር ተማሪውም ለመማር አላስቻላቸውም። ያ እንዳለ ሆኖ ከዓለም ዙሪያ ለዕውቀት ማዳበሪ አዲስ ገኝቶችን ለመቃረም መንገዱን ክርችም አርገው ዘግተውታል። ዘመኑ ሣይንስ ያስገኘውን የዕደ ጥበብ ውጤት ተጠቅሞ ዕውቀትን የሚያስፋፋበት ድንቁርናን የሚያጠፋበት ጊዜ ነው። ዕደ ጥበቡን ተጠቅሞ የዓለም ሕብረተሰብ ከችግር ለመውጣት በብረሃን ፍጥነት ሲራመድ እኛ ገና በኢሊ

ጉዞ ላይ ነን።

ቆመን የጠበቅናቸው የአፍሪካ ሃገሮች የመገናኛ ብዙሃን ተጠቅመው ድንቁርና ሲዋጉ፡ ረሃብንና ቸነፈርን፣ በሽታን ሲያጠፉ እኛ በሰቆቃ አረቋ ውስጥ ነን። እነርሱ በአሁኑ ጊዜ ተማሪዎቻቸውና አሰተማሪዎቻቸው መገናኛ ብዙሃንን በመጠቀም የዓለም ሕብረተሰብ አባል ሆነዋል። internet, you tube twitter, face book, skype, video, radio ,TV etc ዕደ ጥበቡን ተጠቅመው ወራትና ሳምንት የሚፈጁባቸውን ሥፋራዎች በሰከንድና በደቂቃ ደርሰው ለሕዝባቸው የትምህርት አገልግሎት ለመስጠት ችለዋል። ኢትዮጵያ 90 ሚሊዮን የሕዝብ የሚኖርባት በነፃነት ሣይንስ ያስገኘው የዕደ ጥበብ ተጠቀሚ አይደለችም። ሱማሊያ 10 ሚሊዮን ሕዝብ ያላት ግን ተጠቀሚ ናት። የወያኔ መንግሥት በሕጋዊነት ስም ሕገወጥ ተግባር እየፈጸመ ነው።ሰው በመሆናችን ተፈጥሮ የቸረንን የማወቅ መብት በመሣሪያ ኃይል ተቆጣጥሮ ያደነቁረናል። እኛም የፈቀድንለት ይመስላል።ያ አልበቃ

ብሎ በቅርቡ በፓለቲካ ታሐድሶና ለአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ድጋፍ ስም መምህራን እየተገላቱ ነው። አሻፈረኝ ያሉ መምህራን ከሥራ ሲባረሩና አንደአውሬ ሲታደኑ የምናየው ነው። ታሕድሶውን የተቀበሉትም ቢሆኑ ከሥራ ትባረራላችሁ ቤተሰባችሁ ይራባል ተብለው በፍራቻ ላይ ናቸው።ከዓለም ዙሪያ ከሚገኙ የታወቁ ዩኒቭርሲቲዎች የተመረቁ መምህራን በአንድ በታጠቀ የአጋዚ ወታደር ያለፍቃዳቸው ወደ ታሕድሶ እየተገፉ ነው። ይህንን ያየ ወጣት መማርን እንዴት ያየዋል? በተማሪዎችና በመምህራኑ መካከል መናናቅ ይፈጥራል። መምህራን እንደባለሞያ ሳይሆን እንደሥራ ፈት ቦዘኔ አንድ ለአምስት ተጠናፈጉ መባሉ ውርደት ነው።እንኳስ ለሙሑሩ ለሥራ ፈቱ ቦዘኔም የሚመኙት አይደለም። ስለዚህ ተቀባይነት ባለው የሞያው መስክ መምህሩም ያስተምር ተማሪውም ይማር። ታደለ መኩሪያ tadele@shaw.ca

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የጠየቀው ይግባኝ ተቀባይነት በማግኘቱ ለክርክር ተቀጠረ

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ጠበቆቹን አሰናብቶ ራሱ ይከራከራል በታምሩ ጽጌ [ሪፖርተር-ጋዜጣ] በተከሰሰበት የሽብርተኝነት ወንጀል ጥፋተኛ ተብሎ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ ወንጀል ችሎት ሰኔ 20 ቀን 2004 ዓ.ም. በ18 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ውሳኔውን በመቃወም ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያቀረበው ይግባኝ ተቀባይነት በማግኘቱ ለክርክር ለጥቅምት 27 ቀን 2005 ዓ.ም. ተቀጠረ፡፡ የሥር ፍርድ ቤት ያስተላለፈበትን የጥፋተኝነት ፍርድና የቅጣት ውሳኔ በመቃወም ‹‹ንፁህ ነኝ፣ የቀረበብኝ ማስረጃ የለም፡፡ ፍርድ ቤቶች የተከበሩ ተቋማት በመሆናቸውና የበቀል፣ የአፈናና የጭቆና መድረክ መሆን ስለሌለባቸው በነፃ ልለቀቅ፤›› በማለት ነሐሴ 9 ቀን 2004 ዓ.ም. ይግባኝ ማለቱን ለፍርድ ቤቱ ያቀረበው አቤቱታ ያስረዳል፡፡ ጋዜጠኛ እስክንድር በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን፣ ከግንቦት 7 ከፍተኛ አመራሮች ጋር በህቡዕ ግንኙነት በማድረግ ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ስብሰባ በማድረግ፣ የገንዘብ ድጋፍ

ለማድረግ በመስማማት፣ የግንቦት 7 ልሳን ለሆነው ኢሳት መረጃ በመስጠት፣ ቀስቃሽ ጽሑፎችን በመጻፍና በማሠራጨት ወንጀል የመጀመሪያው ክስ ተመሥርቶበታል፡፡ የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 7(2)ን በመተላለፍ ደግሞ የግንቦት 7 አገር ውስጥ ወኪል በመሆን ወንጀል ሁለተኛ ክስ ሲመሠረትበት፣ የወንጀል ሕግ 32 (1/ሀ) እና 248(ለ)ን በመተላለፍ ደግሞ የኤርትራ መንግሥት የሽብር አጀንዳ ለማስፈጸም እንዲመቸውና እንዲቀናጅ በመርዳት ከፍ ባለ የክህደት ወንጀል ሦስተኛ ክስ ተመሥርቶበት እንደነበር ይታወሳል፡፡

ጋዜጠኛ እስክንድር ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረበው የይግባኝ አቤቱታ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ሦስት ክሶች መሥርቶበት አንድ የሰው ማስረጃ፣ የኦዲዮና የቪዲዮ ማስረጃዎችን ያቀረበ ቢሆንም፣ አንዳቸውም እንደ ክሱ እንዳላስረዱና እንዳልተመሰከረበት አብራርቷል፡፡ ዕውቀትና ልምድ በቅጡ ያልዳበረበት የፀረ ሽብርተኝነት ሕግ 652/2001 (23) በተሳሳተ መንገድ እንደተተረጐመ፣ የላባ ያህል ክብደት ያለው ማስረጃ ሳይቀርብበት ጥፋተኛ ለማሰኘት ዓቃቤ ሕግ የተጠቀመበት አግባብ አለመሆኑን እስክንድር በአቤቱታው አስረድቷል፡፡ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ሰኔ 20 ቀን 2004 ዓ.ም. ባስተላለፈበት ባለ 68 ገጽ የቅጣት ውሳኔ ውስጥ ተፈጽመዋል ያላቸውን ስህተቶች በ11 ርዕሶች ከፋፍሎ በዝርዝር ያቀረበው ጋዜጠኛው፣ የዓቃቤ ሕግ ምስክር ሆነው ቀርበው የነበሩት የመኢዴፓ ዋና ጸሐፊ አቶ ዘመኑ ሞላ ‹‹የፋይናንስ ችግር ካለ ከአንተ 20 ሺሕ ብር፣ ከእሱም 20 ሺሕ ብር፣ ከእኔም 20 ሺሕ ብር እረዳችኋለሁ ብሎኛል፤ ከአቶ ፋሲል የኔዓለም ጋርም በስልክ እንደሚገናኙና በፋይናንስ እንደሚረዳውነግሮኛል፤›› ብለው መስክረዋል

በሚል በውሳኔው ላይ የሰፈረው ዓረፍተ ነገር ሐሰት መሆኑን ፍርድ ቤቱ እንዲያይለት ጠይቋል፡፡ ፍርድ ቤቱ የቀረፀው የኦዲዮ ማስረጃ እንዲሰማለትና እሱም ያቀረበው መስቀለኛ ጥያቄ እንዲደመጥለት በማመልከቻው ጠይቋል፡፡ በሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ ሰነድ ላይ ሰፍሮ የሚገኘው የዓቃቤ ሕግ ምስክሮች ቃልና ምስክሮቹ በችሎት የተናገሩት ቃል ያለቦታው እየገባ ፍርድ ቤቱ ለውሳኔ በሚያመቸው ሁኔታ እንደተጠቀመበት፣ ገጹንና የሰፈረውን ቃል ጭምር በመጥቀስ ዝርዝር የይግባኝ አቤቱታ ያቀረበው ጋዜጠኛ እስክንድር፣ ፍርድ ቤቱ በአፅንኦት እንዲመለከትለት ጠይቋል፡፡

መኢዴፓ መስከረም 21 ቀን 2004 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ሊያደርግ በነበረው ሰላማዊ ሠልፍ ዙሪያና በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ከተደረገ ስብሰባ ጋር በተያያዘ ለቀረበበት ክስ፣ በመከላከያ ምስክሮቹና በቪዲዮ ያቀረበው ማስረጃ ከግምት ውስጥ እንዳልገባለት የጠቀሰው ጋዜጠኛ እስክንድር፣ መኢዴፓ ሰላማዊ ሠልፉን እንዳያደርግ፣ ውጭ አገር ካሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ገንዘብ እንዳይቀበሉና ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዳያደርጉ መምከሩን በአስረጂነት ጠቅሷል፡፡ የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔም መሠረታዊ የሆነ ስህተት ስላለበት ኦዲዮውን ፍርድ ቤቱ እንዲያደምጥለት ደጋግሞ ጠይቋል፡፡ በአንድነት ቢሮ ያደረገውን ንግግርና የመራውን መድረክ በሚመለከት ቪዲዮውን መመልከት በቂ ምላሽ መሆኑንም ጠቅሷል፡፡ ጋዜጠኛ እስክንድር በአቤቱታው ላይ አንድነት ቢሮ ተገኝቶ የገለጸው በመሠረታዊ ባህሪያቸው ተፈጥሮአዊ ሆነው በሕገ መንግሥቱም ዕውቅና የተሰጣቸው ዴሞክራሲያዊ መብቶች እየተጣሱ መሆኑን፣ በአፍሪካ አገሮች እየተከበሩ በኢትዮጵያ

አለመከበራቸው ታላቅ አገራዊ ውርደት መሆኑን፣ ለመብቶች አለመከበር ምክንያት የሆኑት ጥቂት የኢሕአዴግ አመራር አባላት በተለይ በኪራይ ሰብሳቢነት የተሰማሩት እንጂ ብዙኅኑ የኢሕአዴግ አባላት አለመሆናቸውን፣ የመሳሰሉት መሆናቸውን በማመልከቻው ጠቅሶ ‹‹ታዲያ ይኼ ምኑ ነው የሚያስከስሰው?›› በማለት ጠይቋል፡፡ በአጠቃላይ የሥር ፍርድ ቤት ያስተላለፈበት የጥፋተኝነትና የቅጣት ውሳኔ ተጨባጭ የሆኑ ማስረጃዎች ሳይቀርቡበት፣ በማመሳሰልና የቃላቶችን አገባብ በማዘበራረቅ መሆኑን በመጥቀስ፣ ፍርድ ቤቱ ንፅህናውን በማየትና የቀረበበት ምንም ዓይነት ማስረጃ አለመኖሩን በማረጋገጥ፣ በነፃ እንዲያሰናብተው ባቀረበው ባለ አሥር ገጽ የይግባኝ አቤቱታ ላይ ጥቅምት 27 ቀን 2005 ዓ.ም. ክርክር እንደሚያደርግ ታውቋል፡፡ ጋዜጠኛ እስክንድር በሥር ፍርድ ቤት ክርክሩን ያደርግ የነበረው በጠበቃ ታግዞ የነበረ ቢሆንም፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሚኖረው ክርክር ላይ ግን ያለጠበቃ ራሱ እንደሚከራከር ታውቋል፡፡ ጋዜጠኛ እስክንድር በይግባኙ ላይ ክርክር ለማድረግ ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሚቀርብበት ጥቅምት 27 ቀን 2005 ዓ.ም. 43ኛ ዓመት የልደት በዓሉንም ያከብራል፡፡ ለአሥራ ስምንት ዓመታት ፅኑ እስራት የተፈረደበት ጋዜጠኛ እስክንድር ለአምስት ዓመታት ከሕዝባዊ መብቶቹ ከመሻራቸውም በላይ፣ የእሱ፣ ዕድሜ ልክ የተፈረደበት አንዱዓለም አራጌና በሌለበት 15 ዓመታት የተፈረደበት አበበ በለው ንብረቶች እንዳይሸጡ፣ እንዳይለወጡና ለሦስተኛ ወገን እንዳይተላለፉ በፍርድ ቤት መታገዳቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡


TZTA: Page 18: October 23, 2012: www.tzta.ca

COMMUNITY CLASSIFIED DIRECTORY GROCERIES & VARIETY STORES

ልዩ ልዩ ዓይነት የምግብና ሸቀጣ ሸቀጥ መደብር

ARADA GROCERY

አራዳ ገበያ

የተለያየቅመማ ቅመምን እናቀርባለን። ገንዘብ ወደ አገር ቤት እንልካለን። የስጦታ እቃዎችን፣ የተለያዩ የቴሌፎን ካርዶች ወዘተ... በቅናሽ እንሸጣለን። ቪዲዮና ካሴት እንሸጣለን; እናከራያለን። ምርጥ ጥሬ ቡና ፣ የእጣን አይነቶችና እንጀራ በሱቃችን ይገኛል።

Tel:-

416-531-4531

GROCERIES & VARIETY STORES

ልዩ ልዩ ዓይነት የምግብና ሸቀጣ ሸቀጥ መደብር

Harar Grocery

1318 B Bloor St. West, Toronto We sell Teff, Barley, Self Raising Flour, Rice, All kind of Spices & Calling Card. ጤፍ፣ ገብስ፣ ሰልፍ ራይዚንግ ዱቄት፣ ሩዝ፣ ሁልም ዓይነት ቅመማ ቅመሞችና ኮሊንግ ካርድ እንሸጣለን።

Call A. Zakaria at:

GROCERIES & VARIETY STORES

ልዩ ልዩ ዓይነት የምግብና ሸቀጣ ሸቀጥ መደብር

WARE GROCERY 440 DUNDAS STREET EAST, TRONTO

ቅመማ ቅመም፣ ሽሮና በርበሬ፣ ኮሊንግ ካርድ፣ ሲዲና ዲቪዲ፣ እንጀራ፣ የተለያዩ ለእንጀራ የሚሆኑ ዱቄቶች፣ ቆሎና ዳቦ እንዲሁም ልዩ ልዩ የግሮሰሪ እቃዎችን እንሸጣለን።ስልክ ደውሉልን፣ ኑና ጎብኙን!!

856 BLOOR STREET WEST, TORONTO ON

Tel;- 647-348-0697 Cell: 647-628-0672

BB SUPER STORE

KULUBI FOOD & SPICE

INGERA DESRIBUTERS እንጀራ ኣክፋፋዮች

We sale Spices, Calling Card, Ingera, DVD & CD and all grocery items. We send money to Ethiopia. ወደ መደብራችን ከመጣችሁ ሁሉንም ዓይነት የምግብ ሆነ የግሮሰሪ ሸቀጣ ሸቀጦች ታገኛላችሁ። ኑና ጎብኙን፣ ስልክም ደውሉልን።

Freta Ingera Services

Ethiopian Spices, Red Chill, Teff, Flour & Other Grain Products

ቢቢ ገብያ ቅመማ ቅመም

* በርበሬ *ሽሮ *ጤፍ *ገብስና የመሳሰሉትን ከሀገር ቤት አናስመጣለን። እንሸጣለን። እንጀራ ጠይቁን ይኖረናል።

Tel: 416-425-4809

2008-2010 Danforth Avenue, Toronto,ON

223 Parliament St. Toronto

Tel: 416-364-0000 416-923-1617

Relators የቤት ግዥና ሻጭ

Relators የቤት ግዥና ሻጭ

ታደሰ ተሰማ

አቶ ሳሙዔል በቀለ Tad Tessema Tel:- 647-649-7532

Sale Representative Direct:Real Estate Brokerage

416-649-7532

For detail info. Call Samuel at: tadtessema@yahoo.com www.tadrealty.ca

416-996-3729 E-mail:-

samuelbekele@gmail.com

Tel:416-551-8537

LIMOUSINE SERVICE የሊሞዚን አገልግሎት HEATING & AIR CONDITIONING SERVICE

አየር ማሞቂያና ማቀዝቀሻ

ARIF HEATING & AIR CONDITIONING

INSTALLATION & REPAIR OF FURNACES AIR CONDITIONING FIREPLACES & BOILER 24 HOURS EMERGENCY Call Haile Mamo

416-995-1244

HEATING PLUS Heating & Air Conditoning Service and Instalation

1111 Finch Avenue West Toronto ON

831 Bloor Street West, Toronto ጥራት ያለው እንጀራ እናቀርባለን። ለተለያየ ዝግጅት ፓርቲ እንጀራ ስትፈልጉ ስልክ ይደውሉልን። ከመጀመሪያ እስከመጨርሻ ምርጫዎ የፍሪታ እንጀራ ይሁን። እንጀራ በትዕዛዝ እናቀርባለን። በተጨማሪ ሽሮ፣ በርበሬአ ቅመማ ቅመም አለን።

*Furnaces *Gas Firplace *Hot Water Tanks *Gas BBQs *Pool Heaters *AC Units *Clean Air System *Humidifications *Stove Lines *Refrigerator Lines *Gas Piping *Duct Cleaning. Call Yoseph Gebremariam

ፍሬወይኒ ክብሮም

www.heatingplus.ca

Tel:-647-342-5355 fretakibrom@yahoo.com

ደስታ ሥጋ ቤት

አመርቂ ምርጥ ምርጥ የስጋ ብልቶች ንጹሕ ቅመም፣ በባለሙያ የተዘጋጀ በርበሬ፣ እቃዎች እንሸጣለን። ገንዘብ እንልካለን። ለተለያዩ ግብዣዎች ምግብ እናቀርባለን። ደስታ ምግብ ቤት በየቀኑ በአመት በዓል ጭምር ክፍት ነው። Tel:-

416-850-4854

843 Danforth Avenue

Tel:-647-404-6755 Renovation/Plumbering

የቤት አዳሽና ቧንቧ ሠራተኛ Wondy Plumbering And Renovation

Plumbering - Paiinting - Dry Wall Flooring Tiles. Remodeling Kitchen & Bath - Install New Rough in Replace foucet/ Installing New Faucet - Change Water Heater, Unclogged Drain, RelocationPlumbering - Fixture Etc... Wondy Tesfaye Tel: 416-875-1801 E-mail: wondy.tesfaye@yahoo.ca “Dedicated to quality of services”

ትዕግስት ካነበበችው የላከችልን

ገንዘብ ሳይከፍሉ ለሰዎች ሊያበረክቱ የሚችሉዋቸው ስጦታዎች

“ትልቅ ነገር ማድረግ ቢያቅተን ከፍቅር ጋር ትንሽ ነገር ማድረግ አያቅተንም” ይላሉ ማዘር ተሬዛ፡፡ በዕለት ተዕለት ውሎአችን ዋጋ (ገንዘብ) የማያስከፍሉ፤ ነገር ግን ለሰዎች እጅግ ዋጋ ያላቸውን ነገሮችን አንድ ያልታወቁ ጸሐፊ እንዲህ አስቀምጠዋቸዋል፡፡ * የመስማት ስጦታ ሰዎች ስለጉዳያቸው ወይም ስለችግራቸው ሲያወጉ ከልብ መስማትን የመሰለ ስጦታ የለም፡፡ ታዲያ ሳናቋርጣቸው፣ በሐሳብ ሌላ ቦታ ሳንሄድ ወይም ስለምንመልስላቸው መልስ ሳናሰላስል መሆን አለበት፡፡ ዝም ብሎ ከልብ ማዳመጥ ብቻ! * ፍቅር የማሳየት ስጦታ ፍጹም ሳይሰስቱ ከልብ ሰዎችን በመጨበጥና በማቀፍ ለእነርሱ ያለዎትን ፍቅር፤ ትኩረትና አድናቆት ይገለጹላቸው፡፡ * የሳቅ ስጦታ በየዕለቱ የሚገጥምዎትን አስደሳች ሁኔታዎች (ጽሑፎች፤ ፎቶዎች፤ ካርቱኖች) በመላክ ደስታዎን (ሳቅዎን) ለሰዎች ያካፍሉ፤ የሌሎችንም ደስታ ወይም ሳቅ እንዲሁ ይካፈሉ፡፡ * የጽሑፍ ስጦታ ሰዎች ስላደረጉልዎ መልካም ነገር ምስጋናዎን በራስዎ የእጅ ጽሑፍ በመጻፍ ይስጧቸው፤ የዚህ ዓይነት ጽሑፎች ዘመን ከመሻገራቸውም በላይ ሕይወት ይቀይራሉ፡፡ * የምስጋና ስጦታ ሰዎች ለሰሩት ሥራ ወይም ላደረጉት ለውጥ “ትልቅ ሥራ ሰርተሻል”፤ “ዛሬ በጣም አምሮብሃል”፤ “በጣም ቆንጆ ምግብ ሰርተሻል” ወዘተ… በማለት አድናቆትዎን ይግለጹ፡፡ ይህን ዓይነት እውነተኛ አድናቆት የሰዎችን ቀን ብሩህ ያደርጋል፡፡ * መልካም ውለታ የማድረግ ስጦታ ከዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎ ወጣ ይበሉና ለሚወዱዋቸው ሰዎች ያልተጠበቀ ድርጊት በመፈጸም ያስደንቋቸው፡፡ አረጋውያንን መጠየቅ፤ ሕፃናትን ማጫወት ወዘተ… * የሰላም ስጦታ ሰዎች ብቻቸውን መሆን በሚፈልጉበት ሰዓት ብቻቸውን እንዲሆኑ በመፍቀድ (በመተው) ሰላማቸውን እንደ ስጦታ ይስጧቸው፡፡ - የበጎ ቃላት ስጦታ መልካም ሰላምታ በመስጠት፤ ለተደረገልዎ ነገር ሁሉ ምስጋና በማቅረብ በመልካም ቃላትዎ የሰዎችን መልካም ስሜት ይጠብቁላቸው፡፡

ጥንታዊው የሙርሲዎች የጆሮ ቅድና የዘመኑ የምዕራባዊያን ፋሽን

በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በኦሞ ሸለቆ ከሚኖሩት የሙርሲዎች ጥንታዊ የጆሮ አበሳስ ባሕል ጋር የሚመሳሰል ፋሽን በምዕራባውያን አገሮች እየተስፋፋ መምጣቱን ቢ.ቢ.ሲ ዘግቧል፡፡ በበለፀጉ አገሮች አውራ ጎዳናዎች ላይ ጆሮአቸውን በሰፊው በመቀደድ ዙሪያውን ብረት መሰል የጆሮ ጌጦች ማድረግን እንደ ፋሽን የተያያዙ በርካታ ሰዎችን መመልከት የተለመደ ሆኗል፡፡ ዶክተር ኬን ስትዋርት የተባሉ የሕክምና ባለሙያ እንደጠቆሙት ጆሯቸውን በሰፊው በመለጠጥ ከሚበሱ ሰዎች መካከል አንዳንዶቹ ቦጆሯቸው ላይ ለሚፈጠር ጉዳት እስከ 8 ሺሕ ፓውንድ በሚደርስ ወጪ የማስተካከያ ቀዶ ጥገና ሕክምና ጆሮን በሰፊው ለጥጦ መብሳት በአገራችን በሙርሲዎች ዘንድ የቆየ ባሕል ሲሆን በተመሳሳይ በሌሎች የዓለም ክፍሎችም ከጥንት ጀምሮ የተለመደ ባሕል እንደሆነ ታሪክ ይጠቁማል፡፡ ለምሳሌ የ5300 ዓመት የሚገመት ዕድሜ ያለውና ኦዚ ዘ አይስ ማን የተባለው የሰው ዘር ቅሪተ አካል እንደጠቆመው ተመሳሳይ ጆሮን የመለጠጥ ባሕል በወቅቱ ተግባራዊ ይደረግ እንደነበር ለመረዳት ተችሏል፡፡ እንዲሁም የቡድሃ እምነት ሃውልቶች ተመሳሳይ ልማድን የሚያንፀባርቁ ሲሆን በሰሜን ታይላንድ የሚኖሩ ጎሳዎችም ከጥንት ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ጆሯቸውን በሰፊው የመበሳት ባሕል ተግባራዊ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ይህ ልማድ በአንዳንድ የዓለም ክፍሎች የአንድ ግለሰብ መንፈሳዊነት መገለጫ ሲሆኑ በሌሎች ደግሞ ግለሰቡ በኅበረተሰቡ ዘንድ ያለውን የክብር ደረጃ የሚጠቁም ነው፡፡ - ቢ.ቢ.ሲ (ኖቬምበር 21 ቀን 2011)

የአጤ ምኒልክ የአገር ውስጥ ደብዳቤዎች

• ይድረስ ከአዛዥ ወልድ ጻድቅ ለደብረ ብርሃን ሥላሴሰ ቤተ ክርስቲያን ሥራ የኖራውን ነገር የአንተ አገር ሰው ቆለኛ ቆለኛው ይቻል ብያለሁና ኖራ በብዙ ቶሎ እንድታስመጣ ይሁን፡፡ መስከረም 18 ቀን 1900 ዓ.ም. አዲስ አበባ ተጻፈ፡፡ • ይድረስ ከአዛዥ ግዛው ከእቴጌ ቅጥር የተረፈውን ጠርብ ለኖራ ማስቀመጫና ለእንጨት መሥሪያ ልሥራ ያልከውን ምን ከፋ፡፡ ጠርቡ እንዳይቆራረጥ ለኋላ ሥራ እንዲይዝልን ይሁን እንጂ አሁንስ አንተው እንዳልከው ለዚሁ ለኖራው ማስቀመጫና ለእንጨት መሥሪያ ቤት እንዲሆን አድርገህ ማሠራት ነው፡፡ • ይድረስ ከፊታውራሪ ወሌ ደብዳቤህም ደረሰልኝ፡፡ እግዚአብሔር እንኳን ከዘመን ዘመን አብሮ አሸጋገረን፡፡ ደግሞ እንደዚሁ ለዘመነ ማቴዎስ በደኅና ለመድረስ ያብቃን መስከረም 27 ቀን 1900 ዓ.ም. ተጻፈ፡፡ ጳውሎስ ኞኞ ‹‹አጤ ምኒልክ በአገር ውስጥ የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች››(2003)

‹አምስት ደቂቃ ወደ ገሀነም ነበር የምልካችሁ››

በአንድ ቃለ መጠየቅ ላይ በግብ ጠባቂነት ለረጅም ጊዜ ያገለገለን አንድ ኳስ ተጫዋች ‹‹በረጅም ጊዜ የኳስ ሕይወትህ ምን የሚጸጸትህ ነገር አለ?›› ተብሎ ቢጠየቅ፣ ‹‹በጣም የሚጸጽተኝ ነገር ቢኖር ላድናቸው ስችል የገቡብኝ ጎሎች ናቸው፤›› ሲል መለሰ፡፡ የግብ ጠባቂው መልስ የደኅንነት ሠራዊት መሽራች የሆኑት ዊሊያም ቡት (1892- 1912) አንድ ጊዜ ለተማሪዎቻቸው ‹‹ምርጫ ባገኝ ኖር እናንተን ወደ ትምህርት ቤት ሳይሆን ለአምስት ደቂቃ ወደ ገሀነም ነበር የምልካችሁ፣ በእውነት ለነፍሳት ግድ የሚላችሁ ሆናችሁ ትመለሱ ነበር፤›› ያሉትን ያስታውሰኛል፡፡ ወደ ሲዖል ሲቻኮሉ እንዲመለሱ ምክንያት ልንሆንላቸው የምንችል ስንት ሰዎች አምልጠውን ይሆን? ኃይለ ከበደ ‹‹ምስካይ›

ንቃ ንቂ ንቁ

በነፃ የታደሠው አዲሱ ትውልድ እየመጣ ነው፡፡ በመታነፅ በታደሰው አዳሽ እወጃ አዲስ ትውልድ ውስጥ የሰውን ልጆች ሁሉ አንድ የመሆን የሚያበሥረው እውነት ነፅሮ ይወጣል፡፡ በተለያዩ ሃይማኖቶች መካካል ያለው የመቃቃር ጉጥ አዘል ልዩነት ይከስማል፡፡ በሁሉም ሃይማኖቶች ውስጥ የሚንፀባረቀው የተቀደሰ በጎ ፍሬ ይቀጣጣላል፡፡ የሰው ልጆች ልብ በፍጥረታት ሁሉ ፍቅር በመንደድ እስኪሞላ ድረስ ይህ ይሆናል፡፡ እናም እኒህ ተጠቃሽ ኅብራዊ ክንዋኔዎች የሰው ዘርን የጋራ ግብ ወደሆነው ፍፁማዊ በኀነትና መልካምነት ያመጡታል፡፡ አሁን በምንለው በዚህ በዛሬው ዘመን ለመምረጥ የሚያስችል ጉልበት አለህ፡፡ ፍቅርን ምረጥ ጥላቻን ግን አይደለም፡፡ ጨዋነትን ምረጥ በጡንቻ ማመንን ግን አይደለም፡፡ ቅድስናን ምረጥ ክፋትን ግን አይደለም፡፡ ፍቅርና ሰላም በፍጥነት እየመጣ መሆኑን ለማመን የሚያስችል ድፍረትና ቆራጥነት ይኑርህ፡ ፡ ይህንን በግስጋሴ ላይ ያለውን ፍቅርና ሰላም ተቀብሎ ለማስተናገድ ከወዲሁ ራስህን አዘጋጅ፡፡ እውነተኝነት ወይም እና ፃድቅነት በር ከፍች ነው፡ ፡ ተግባራዊነቱ ባልተጓደለ እውነተኝነትና ፃድቅነት ተሞልተህ ፍቅርና ሰላምን በመቀበል ተዘጋጅ፡፡ እውነተኝነት ወይም እና ጻድቅነት በር ከፋች ነው፡ ፡ ከበሩ በላይ ፍቅር አለ፡፡ መለኮታዊው ኃይል በሕይወትህ ሁሉ ባሉ ሁለንተናዎች በምልዓት ሊገባ ይፈቅዳል፡፡ ለቁሣዊ ነገርህ ጭምር ወሮታውን ይከፍላል፣ ይሸልማልም፡፡ ይህ ተገላጭ ቅዱስ መንፈስ በምክንያት ለተፈጠረ ፍጥረት ሁሉ ጠቃሚ ጉልበትን እንቀሳቃሽ ኃይል በመስጠት ለዘላለማዊውን የመንፈስ ብርኀን ለማፍሰስና ለመልቀቅ ከመቼውም ይልቅ እጅግ አድርጎ በተቃረበበት ምዕራፍ ላይ እንደምትሆን እወቅ፡፡ ከበደ ደበሌ ሮቤ ከዳግማዊ ዴዜሬራታ ወደ አማርኛ የመለሰው ‹‹ወርቃማ አዲስ አበባ›› (2000)


TZTA: Page 19 : October 23, 2012: www.tzta.ca

Address by Minister Baird at Inter-Parliamentary Union Assembly

In my time as foreign minister, I have directly confronted some of these people, and I’ve done so because there are times when diplomacy must be balanced with tough, direct talk.

We may share a mother tongue but practice a different faith.

We may share a religion but come from different cultures. Yes, we may have a thousand differences, but we all share one humanity. Sadly, there are forces of evil in this world that use our differences as weapons to marginalize minorities, often calling for violence against them.

Minister Baird October 22, 2012 - Québec Good morning. I’m honoured to address this year’s assembly of the Inter-Parliamentary Union [IPU]. Today’s debate on diversity is an important one and one that is ever more important given the turbulence and uncertainty we see in many corners of the world. As we stand on the threshold of the next century, we are reminded of that old adage, “the only constant is change.” When change is swift and unexpected, it is all the more important that we focus on the constant that remains true: that people everywhere will fight for dignity. The dignity to live in freedom. The dignity to live in peace. The dignity to provide for one’s family. In the current and raging storm of change, societies that are free, open and democratic stand as beacons of light. We know what it takes to build the conditions in which people live with the dignity they crave. We know that freedom, democracy and human rights are the values upon which pluralistic societies are built. But we also know that pluralism will not flourish unless we embrace the diversity of our societies. As Michel de Montaigne said, “there never were in the world two opinions alike, no more than two hairs or two grains; the most universal quality is diversity.” Indeed, as I look around this room, I see a reflection of the true diversity of our global community. A reflection of that truism that even though our faces are composed of but 10 parts, in a room of thousands, we won’t find two the same. We may share the same colour of skin but speak different languages.

This is where we, as free societies, have a role to play. The great poet Kahlil Gibran inspired us to remember that “safeguarding the rights of others is the most noble and beautiful end of a human being.” This is not simply a question of beliefs and values. It is a requirement for action. Protecting human rights and human dignity is an obligation that each state owes its citizens and a mutual obligation of all members of the international community. History teaches that an open society—tolerant, pluralistic and free—is the best guarantor of human rights and dignity. Often, a threat to the security of humankind is coupled with the crushing of human rights.

little fighting chance of obtaining an education.

As children, they are not ready to be parents themselves. Their bodies are not ready to birth children, and, when they do, they often die in labour, have sickly, premature babies and are more likely to get AIDS. It’s a vicious cycle that repeats and repeats and repeats as long as we don’t end it. Our government is standing up for these girls, even when it’s not always expedient to do so. We don’t shy away from such tough conversations. And in these conversations, I have been shocked when other countries have called me culturally insensitive for raising this. Well, you know what? I am going to talk about it. I’m not going to stay quiet on an issue that is morally wrong and deserves to be condemned. How can anyone defend the practice of having a nine-year-old girl forced into marriage? If Canada—a free and open society that respects human rights—won’t speak up for these girls, who will? I recognize that it’s not a problem that developed overnight; this is ages old, and it won’t be solved overnight.

Yet human rights abuses that don’t threaten security still concern us.

But it’s time for the global community to demonstrate a real commitment to change, not just in words, but also in action.

The enslavement of others is a vicious human rights abuse, and it takes many forms. Too often, women are particularly vulnerable to the gravest of abuses.

That’s why Canada will continue to speak up and work with others to end this practice. This builds on important work we have been doing at the UN Human Rights Council on this issue.

For example, the early and forced marriage of young girls—a truly barbaric form of slavery.

And work being done by my colleague Rona Ambrose [Minister of Public Works and Government Services and Minister for Status of Women]—whose dedication to the issues facing women and girls around the world has led Canada to spearhead the International Day of the Girl.

Speaking truth to power. I do so, standing firm on the principles that have made Canada economically prosperous and rich with diversity. Yet, too many countries currently have regressive and punitive laws on the books that criminalize homosexuality. In some countries, these laws are unenforced hangovers from a bygone era. In others, they are actively and viciously implemented. Draconian punishment and unspeakable violence are inflicted on people simply for whom they love and for who they are. People like David Kato. David worked tirelessly as an advocate for Sexual Minorities Uganda, an organization fighting for full legal and social equality for gay people in Uganda. Its work is exceedingly difficult. Fear for personal safety and the likelihood of being ostracized by society is a daily reality for gay people in that country. Against those odds, David faced constant death threats because of his work and his sexual orientation. In 2010, a Ugandan tabloid newspaper published on its front page the pictures and names of known homosexuals in that country, with a headline that beamed “Hang Them.” David was in one of those pictures.

Every year, millions of girls are forced into marriage, some as young as 9 years old. In the two hours we will have spent here, 2,200 children will be forced into early marriage. Girls like Habiba, a child bride in Niger who was forced into marriage at 14 years of age. At 15, she became pregnant, having to labour for two days before being transferred to a regional hospital to receive a Caesarean. Sadly, she lost her baby hours after he was born, when a simple procedure could have saved his life. Her husband left her, and her village rejected her. Today she lives with her mother. Completely ostracized, she no longer leaves her home—not even to get water. For girls like Habiba, the journey from girlhood to womanhood is too fast and too brutal. No girl deserves to be robbed of her childhood. When girls as young as nine years old are forced to marry against their will, they have

We will intensify our diplomacy and development work to end early and forced marriage in every corner of the world. I call on each and every one of you to do the same. As citizens of a global community, we have a solemn duty to defend the vulnerable, to give voice to the voiceless, to challenge the aggressor, and to promote and protect human rights and human dignity, at home and abroad. Speaking out when we see hate and violence also means we cannot be selective about which human rights we defend, nor can we be arbitrary about whose rights we protect. Sadly, this is something lost on too many people who hold power.

MEAT MARKET WHOLE SALE & RETAIL RESTAURANT SERVICE

Last year, in his own home, David was brutally bludgeoned to death with a hammer. His life and death is but one tragic story, in but one country. It is cases like his that drive me to raise this issue, often to the discomfort of the people sitting across the table, as I did at recent meetings in Australia and New York. In these meetings, Canada was the loudest voice. I called on my colleagues to repeal regressive laws in their own countries because I firmly believe it is the role of the state to protect its people regardless of sex, sexuality or faith. These are issues which, in the past have rarely been raised by Canadian governments—if ever. Yet we are. We’re working with allies like the EU and the United States on encouraging the decriminalization of homosexuality. We’re working with all political parties in the House of Commons to fight those who restrict basic human rights, from Kampala to St. Petersburg. These are small victories. But ones that come Continued on page 23


TZTA: Page 20: October 23, 2012: www.tzta.ca We believe what’s right is right. from honestly good intentions. We will speak out on the issues that matter to Canadians—whether it is the role and treatment of women around the world, or the persecution of gays, or the cowardly and targeted attacks of those who pray in sanctity of churches, temples, mosques or synagogues. Canada will speak out. Since our government promised to open an Office of Religious Freedom, there has been considerable media interest. Critics claim we’re mixing politics and religion. They fail to see that this has nothing to do with mixing politics and religion and everything to do with defending fundamental human rights. Think of it this way: if you pick out any terrorist attack in recent memory where the victims of these attacks were targeted because of their religious beliefs, you’ll find the attacks came from thugs opposed to democracy. Every single time. The late U.S. President [Franklin Delano] Roosevelt once said that “where democracy has been overthrown, the spirit of free worship has disappeared. And where religion and

democracy have vanished, good faith and reason in international affairs have given way to strident ambition and brute force.” The regime in Iran is one poignant example of religious intolerance. Bahá’ís and Christians are consistently threatened with death and torture, simply for believing. Just two months ago, Iran imposed a 20-year sentence on seven Bahá’í leaders who have been in prison since 2008. In 2010, no evidence was produced at the summary trials, and yet they were convicted for a series of national security crimes. A Jewish-Armenian couple was secretly executed in [Iran’s] Evin prison in March. Their only crime appears to have been practising their faith. Canada won’t stand still in the face of these egregious actions. That’s why we have applied some of the toughest sanctions against this regime and why we are committed to defending religious freedom in Iran and around the world. That’s why Canada has led a human rights

resolution on Iran at the United Nations for the past eight years—one that is gaining in support. When you return home at the conclusion of this conference, I urge each of you to work with your government to support our resolution. Canada will continue to do its part. Our government will establish an Office of Religious Freedom in short order. This office will signal to the world that Canada attaches great importance to religious freedom, and we will speak out when we see persecution of religious minorities. We will give voice to the voiceless. Few people can change the course of history, but each of us, working toward furthering human dignity, respect and tolerance, will be able to write the history of our generation and build a foundation for the world we leave behind. It is that conviction that drives us to stand up for the rights of women, who, in too many countries, are assaulted for wanting nothing more than to be treated equally. It is that conviction that drives us to stand up to those who seek to criminalize homosexuality.

And what’s wrong is wrong. And it is in defence of those beliefs that we act. As parliamentarians, we must remember that these are not partisan issues; they transcend politics. I promote our principled foreign policy knowing there is broad support to give women a bigger role in societies where people are free to be and free to practise. As parliamentarians, we ought to be doing the same. We ought to embrace the diversity of our societies, to draw strength from differences. This may sound like an impossible task, but we can take inspiration from Carl Sandburg, who once said that “nothing happens unless first a dream.” The dream is there. Now, we as parliamentarians, have a collective responsibility—to act to make our dream, and the dreams of the people we represent, real. Thank you.

GOVERNMENT OF CANADA CELEBRATES INTERNATIONAL DAY OF THE GIRL

TORONTO, ON – On behalf of the Honourable Rona Ambrose, Canada’s Minister of Public Works and Government Services and Minister for Status of Women, Ms. Roxanne James, M.P. (Scarborough Centre), attended an event in Toronto to celebrate October 11 as the first-ever International Day of the Girl. International Day of the Girl will make a difference in the lives of girls and young women, as citizens and as powerful voices of change within their families, their communities and their nations,” said Minister Ambrose. “My hope is that all Canadians will use this opportunity to rally support for girls’ rights, and to educate the

world about the vast potential of girls to help create a better life for all." In honour of International Day of the Girl, Ms. James delivered opening remarks at an event hosted by Plan Canada and the Toronto District School Board’s “Young Women on the Move” program. Canada is proud to have led the international community in establishing International Day of the Girl,” said Ms. James. “The Government of Canada is committed to improving the lives of girls and women. Since 2009, through Status of Women Canada, our government has approved more than $8.2 million in funding for girl-focused projects.”

In addition, to celebrate the inaugural International Day of the Girl, and as part of its Because I am a Girl initiative, Plan Canada is hosting a day-long public event at Yonge-Dundas Square, including an evening concert. Plan Canada is also holding A Night for Girls to Shine. International Day of the Girl aims to promote equal treatment and opportunities for girls around the world in areas such as law, nutrition, health care, education, training, and freedom from violence and abuse. Throughout the world, girls face higher rates of violence, poverty and discrimination. International Day of the Girl focuses on finding ways to empower

girls to reach their full potential and to overcome gender-based barriers. On December 19, 2011, the UN General Assembly formally adopted the resolution designating the International Day of the Girl. October is Women’s History Month in Canada. In honour of the first-ever International Day of the Girl, the theme for Women’s History Month is Strong Girls, Strong Canada: Leaders from the Start. For information on International Day of the Girl and on Women’s History Month 2012, go to women.gc.ca.

አቶ አምደጽዮን ከበደ 1972-2012

አቶ አምደጽዮን ከበደ ከአባቱ ከአቶ ከበደ ደረሰልኝ ከእናቱ ከወ/ሮ ዘነበወርቅ ትርፍአገኘሁ በአዲስ አበባ ከተማ በንፋስ ስልክ በ1972 እ. አ. አ. ተወለደ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርትን በተባበሩት መምህራን ት/ቤት ከአጠናቀቀ በኋላ የሁለተኛ ደረጃ ትምሕርቱን ደግሞ በኩየራ አድቬንቲስት ሚሺን ተከታትሎል። እንዲሁም በተግባረእድ ቴክኒክ ኮልጅ አጠናቆል። አቶ አምደጽዮን ከበደ ገና በወጣትነት እድሜ በነበረው የስራ አከባሪነት አና ችሎታ ከቤተሰቡ ጋር በመሆን በኢትዩጵያ የተሳካ የግል ደርጅት በማንቅሳቅስ በአራአያአነት የሚጠቅስ ተግባር አምደጽዮን ከወ/ሮ ሂሩት መኩሪያ ጋራ ትዳርን በመመስረት የአንደ ወንደ እና የአንደ ሴት ልጅ አባት ሆኖል። ለትዳሩ የነበራው አክብሮት እና ፍቅር በአራአያነት የሚጥቅስ ነው። አቶ አምደጽዮን ከበደ 2001 እ. አ. አ. ወደ ካናዳ በመምጣት በአጭር ጊዜ የተሳካ ህይወት ለመመሰረት በቅቷል። ለዚህም መስረቱ ለስራ የነበረው ፍቅርና ችሎታ፣ ጠንካራ ቤተሰባዊ እና ማህበራዊ መሰተጋብር መሰረቱ ነበረ። የራሱንና እና የቤተሰቡን ህይወት በሚገባ ከመምራት ባለፈ ወደ ካናዳ እዲስ ለሚመጡ በሩን በመክፈት በማቋቋም፤ በኑሮና በጤና ችግር ለገጠማቸው፡ በመጠየቅ እና በመደገፍ ሙገሳና ምሰጋና ሳየሻ ላከናወነው ተግባር ብዙዎች የሚመሰከሩት ነው። ለቤተስቡ አሰባሳቢና አስታዎዎቂ ነበር። አቶ አምደጽዮን ባደረበት ድንገተኛ ህመም በቶሮንቶ እና በባንኮክ ልዩ ልዩ ሆስፒታሎች በህከምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በአርባ አመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቶል። የቀብር ስራአቱም በአዲስ አበባ ቅደስተ ስላሴ ካታድራል ተፈጽሞል። ባለቤቱ ወ/ሮ ሂሩት መስፍን ልጆቻ ችው አብኔዘር እና ቤዛዊት፣ እህትና ወንደሞቻቸው፣ የቤተሰቡ አባላት በዚህ መሪሪና አስደንጋጭ የሃዝን ወቅት ከጎናችን በመሆን ላጽጽናናችሁን ሁሉ እግዚአብሄር ይስጥልን! እናመስግናለን።


TZTA: Page 21 : October 23, 2012: www.tzta.ca

Ontario’s Conservation Officers Patrolling the Web

Co with calf moose Ontario’s conservation officers spend much of their time patrolling the lakes, trails and back roads of the province’s great outdoors, both near and far. What you may not know is that they are also experienced cyber sleuths. Increasingly, conservation officers are using the Internet as a special investigative tool. While the Internet is a wonderful medium for

sharing information, it can also be used to facilitate illegal activities, such as the illicit trade in wildlife. This means officers conduct more and more cyber crime investigations. Conservation officers now actively monitor the Internet and track down people who are using the web for the purpose of trafficking in Ontario’s fish and wildlife. They pay particular attention to wildlife trade on major on-line classified websites like Kijiji, eBay and Craig’s List. In fact, officers have found people using the Internet to buy and sell such things as angler-caught fish, wildlife taxidermy and wild animal parts, such as skulls and meat. They have even come across people trying to sell live animals, including raccoons, skunks, amphibians and reptiles. This includes a number of cases that involved the illegal trade in endangered species.

Acupuncture and Back Pain

By Dr. Cao Back pain is one of the most prevalent reasons people seek health care. Millions of working days and countless hours of activity and fun are lost each year due to back pain. Common Causes of Back Pain Treated with Acupuncture One of the top causes of back pain are sprains (over stretching one or more of the ligaments in the back) and strains (a rip or tear in the muscle caused by sudden force). This can happen from an injury, poor posture, or improper lifting. Another source of back pain comes from a herniated disc which is a disc that bulges out from its place between two vertebrae. Sciatica is another common form of back pain. Sciatica is a term used to describe pain that extends down into the buttocks and leg which comes from an irritation of a larger nerve in the lumbar spine called the sciatic nerve. Sciatica can accompany sprains, strains, herniated discs as well as back pain emanating from other sources. Traditional Chinese Medicine's (TCM) vocabulary is very different from Western medicine. TCM differentiates patterns of back pain. Common TCM patterns include: * pain that comes from deficiency; * pain that comes from "qi" (vital life energy in the body, pronounced "chee" ) and blood stagnation; * and pain due to cold damp obstruction. Pain that results from deficiency is usually dull, chronic, and improves with rest. It is more common in middle aged and elderly people. Pain from stagnation is more severe and stabbing in nature. There is stiffness and tightness in the muscles and it worsens with rest. Often this type is seen in occurrences of acute sprains and strains. It can reoccur chronically, thereby indicating an underlying deficiency. Pain from cold damp obstruction is worse in the morning, exacerbated by cold and damp weather. It improves with heat and may be

accompanied by numbness, swelling and a sense of heaviness. Traditional Chinese Medicine as Treatment for Back Pain TCM works to restore harmony and energetic balance to the body which stimulates natural healing and promotes health. Acupuncture is one of the primary modalities used and treatment is individual to each patient. When your practitioner treats your back pain with acupuncture, both local (at the site of pain) and distal (away from the area of pain) needles can be used to help resolve the problem. Distal points are very important, especially in acute pain. Often, needles can be placed in areas other than the back and you can get excellent and quick relief. There are many local points on the back and often a practitioner will palpate your body to find the most sensitive spots and needle those. Other adjuncts to treatment might include: electric stimulation of points, and cupping. Generally, it is advisable to have frequent treatment initially and taper off as the pain diminishes. Herbs can also be helpful in moving blood and reducing inflammation as well as strengthening a deficient condition. In a Swedish hospital study with patients who experienced chronic low back pain, doctors concluded that acupuncture provided long term pain relief. They also observed improvement in activity levels, better sleep, and consumption of significantly fewer analgesics for the acupuncture group as compared with the group receiving a placebo treatment. Acupuncture continues to gain popularity in this country because it is an effective treatment of acute and chronic backache. Acute pain can often be cleared up in a few sessions. More treatments may be needed if there is an underlying deficiency, or reoccurring problem, or sciatica. For More information Call Dr.Cao C.M.D. Ac. Prof @

416-225-8099 Or visit us online www.drcao.com

The sale of Ontario wildlife – whole or in parts, alive or dead – is generally illegal and those prosecuted face significant penalties. It is also against the law to possess without a licence or permit most reptile, amphibian, mammal, bird and even some insect species.

trafficking. The Fish and Wildlife Conservation Act provides for penalties of up to $100,000 and two years in jail for persons convicted of these types of offences. Even heftier fines of up to $250,000 and a year in jail are possible under the Endangered Species Act. What can you do about illegal fish and wildlife trafficking, whether on the web or in the wild? Report natural resources violations by calling 1-877-TIPS-MNR (8477667) toll-free anytime or contacting your local ministry office during regular business hours.

Ontario’s Turtles are at risk from illegal for trade

The Ministry of Natural Resources enforces the laws against this illegal

You can also call Crime stoppers anonymously at 1-800-222-TIPS (8477).

አንዋር ቅመማ ቅመም የምሥራች

የተለያዩ የኢትዮጵያ ቅመማ ቅመሞች፣ ቡና፣ የኢትዮጵያ እንጀራ ወዘተ... በጅምላ በተመጣጣኝ ዋጋ እንሽጣለን።

ቡና

በርበሬ

የኢትዮጵያ እንጀራ

የተለያዩ ቅመማቅመሞች

Tel: 416-283-3254 * Cell: 647-859-4339 * Fax: 416-284-8189 E-mail:- anwarabdo2003@yahoo.ca


TZTA: Page 22 : October 23, 2012: www.tzta.ca

Ethiopian Association in GTA and Ethiopia: Time for a Paradigm Shift Surrounding Regions 1950 Danforth Avenue, Toronto, Ontario, M4C 1J4

JOB POSTING Raising Sexually Healthy Children (RSHC) Community Coordinator This position is contract approximately ten hours per week.Hours may vary from week to week depending on project activities. Ethiopian Association in the Greater Toronto Area and the Surrounding Regions is a non-political, non-profit, independent, community-based organization. The Association is committed to facilitating the full participation of all persons of Ethiopian origin in the social, cultural and civic life of Canada, and to the preservation and promotion of their rich and diverse cultural heritage. The Association’s programs and services are provided without discrimination on the basis of race, gender, sexual orientation, age, ethnic origin, creed, religion, political affiliation and physical or mental disability. Project Name: Building Capacity in African Families and Communities through Raising Sexually Healthy Children Peer Parent Leadership Training Funder: Ontario Trillium Foundation Sponsor Agency: Africans in Partnership Against AIDS (APAA) Advisor: Toronto Public Health Project Date: October 1, 2012 – July 30, 2014 Duties and Responsibilities: • Recruit 10 Parent Peer Leaders (PPLs) for RSHC training in the GTA’s diverse Ethiopian community • Book and arrange training venues and prepare resources for training sessions • Keep record of registration, attendance and evaluation forms at each workshop • Assist the trainer from Toronto Public Health with training sessions • Attend a monthly Project Work Group Meeting to report on the progress of project and to work jointly with other Community Coordinators • Look for opportunities for PPLs to outreach to their respective communities, develop outreach timetables for PPLs to facilitate workshops/ formal discussion groups. • Assist the Project Coordinator in promoting the project • Assist with organizing graduation ceremony Qualifications: The successful candidate must possess the following skills & qualifications: • Self-motivated and good team player with the ability to function with minimal supervision • Relevant experience in working with parents or related field with exposure to issues that affect Ethiopian families • Excellent spoken and written language skills in Amharic and working proficiency in English. Knowledge of other Ethiopian languages is an asset • Good knowledge of the Ethiopian community in GTA and Surrounding Regions • Proficiency in Microsoft Word/Word Perfect, email • Skill and experience in community outreach Working Conditions: • May require off- site work • May require evening and weekend work How to apply: Please send your confidential submission quoting in the subject line RSHC including cover letter and resume via sporro@ethiocommun.org or Fax: 416 694 8736 to The Hiring Committee by 5 PM October 28, 2012, We thank all those who apply, but we will respond only to those who are selected for an interview. Ethiopian Association in GTA and Surrounding Regions is an equal opportunity employer.

By Zelalem Eshete

leader.

It takes two to tango. The government’s talk about democracy appears to deal more with the image of democracy than with the reality of democracy. The opposition’s talk about democracy seems to be targeted more at assuming power by whatever means than at providing an alternative unified option for the people to choose. That is the drama of democracy played everyday in Ethiopia. The question is, how can we abandon the drama and get on with the real thing? In this part one of my article, I would focus on the opposition.

Unless you win on those fundamental rights, how can you make conversations about your programs in the first place? Since you are committed to a peaceful struggle, the first strategy is to have the environment that can nurture your non-violent struggle towards implementing your programs.

The political climate on the ground is squeezing the opposition with each passing day. To make things worse, the opposition itself is weak due to divisions, and forgoing leadership it settle for mere opposition. The opposition has to go through rebirth; otherwise it will soon become a do-nothing force as far as peaceful struggle is concerned. I argue that the opposition is not at the mercy of the government regarding its significance. It is within the grasp of the opposition to chart the way and hold the government accountable for the progress or lack of democracy in Ethiopia. The people have spoken about the need to be united and to be purposeful. The opposition leaders echo the need for unity and reinvention. But how can it be done? I would like to share some reflections as to how to achieve the rebirth of a divided opposition that can transform how politics is played in Ethiopia. I hope this attempt might change the public discourse from merely talking about the condition of the opposition to discussing practical how-to steps for achieving genuine progress.

The odds were against you when you were divided. Now that you are united, it is wise to prioritize your actions. You cannot go for everything you want with one shot. The first priority is given to the single vision of the single United Front. That is your united voice. Then you have the second priority, which is holding a dialog over different solutions presented by the interested groups that constitute the single United Front. You try to win together, not fight and destroy each other. This approach requires you to work together now, and also to be prepared to govern together in the future, and even to work alongside of the present ruling party on matters of national interest. We all need each other for this to work. Remember this journey together is all about a peaceful struggle. Therefore, the parties involved should unite on this basic principle and act accordingly. The single United Front will be on a mission towards a non-violent struggle for freedom of speech and press, freedom to organize, and free and fair elections to name a few. The united non-violent struggle for such a cause, while the member parties are conducting their political work at the grassroots level, undoubtedly empowers the member parties to relate their program to the people. This non-violent struggle requires that most of the action take place in Ethiopia. The Diaspora needs to play supportive role in one voice as those on the front line assume the primary responsibility.

The Political Landscape of the Opposition Strategic Organization and Leadership The political landscape of the opposition in Ethiopia is characterized by three major sectors: those who are pursuing peaceful struggle in Ethiopia, those who are taking the armed struggle to Ethiopian government, and the Diaspora organizations that are trying to have their input on Ethiopia’s future. Each one is calling for unity, which actually is a call that serves its own end. Each one is calling the other to join itself. Each one is facing dual challenges: first against the government, and second against each other. Imagine a paradigm shift in how all the groups do business. Imagine each group getting out of its comfort zone, redefining its purpose and reorienting its agenda with the grand vision in sight. I ask the impossible: each group should surrender its selfserving quest for power and instead aim to be an instrument of unity for divided Ethiopia. Some say, “Dream on…” First, I ask the militant opposition to reorient its agenda and give peace a chance. I argue that nothing in the order of this magnitude has been tried in Ethiopia. Therefore, abandon violence and join your brothers and sisters in a peaceful struggle. If you do so, then all opposition parties will be committed to a peaceful struggle without distractions. Second, I ask the opposition engaged in a peaceful struggle at home to reorient its agenda and to form an alliance with all opposition parties at home. Instead of marching ahead with your own goals, find a greater cause to make room for all. Bring on your strength to the table in formation of a single United Front. Third, I ask the Diaspora opposition organizations that are struggling for unity to reorient their agenda and to take on a supportive role for the single United Front. Instead of creating parallel organizations here and there, be the one that empowers the single United Front that has a base in Ethiopia – where the action is. Strategic Vision and Mission A look at the state of the opposition shows not only the difficulty but also the hope for the opposition. We are all stuck at the first observation that the opposition is hopelessly divided and throw up our hands with despair and frustration. But a closer look reveals that there is an opportunity in disguise – if there are any takers. The fact that the opposition is divided, each with a different program should give us a clue that this is not where one should start to seek unity. Instead, we should look for what the common denominator of the oppositions is. The big mistake is to try to mobilize the opposition towards a single unifying slogan of overthrowing the government by whatever means, fueled by hate. That is negative energy. That is the way to win in a violent struggle; it doesn’t work in a peaceful struggle. Therefore, I suggest that you find a voice that all Ethiopians stand behind, including even those who are pro-government at the moment. Do the first thing first, find the one voice that all can speak in one accord for the betterment of Ethiopia. Fortunately, you have that voice that resonates with every one: develop human and democratic rights in Ethiopia. That is where you find your unity. Create a United Front on that vision alone and stand behind one

There has to be a distinction between voting members and supporting members of the United Front. The voting members are the ones who reside in Ethiopia and can participate in Ethiopian elections. The supporting members refer to the Diaspora, which cannot participate in the Ethiopian elections. You don’t have to start from scratch. You can use the organizations that are already functional both in Ethiopia and abroad towards the formation of the single United Front. The delegates from the member parties who are in Ethiopia will constitute the leadership council of the single United Front. The delegates from support organizations of the Diaspora form support chapters in each geographical area. You shouldn’t try to merge all the different programs you are fighting over into one that is not real. Unity in diversity should be your goal, not unity in uniformity. At the same time, don’t get stuck with numerous overlapping parties under the single United Front for long. True, at the beginning all opposition parties in Ethiopia and the Diaspora at large are invited to be voting members and supporting members of the single United Front respectively. At that time the numerous opposition parties that are engaging in the election process or planning to engage in the election process in Ethiopia become what I call “member parties” under the umbrella of the single United Front. However, the strategic goal is not to stay there, but evolve further. You start taking a hard look at the numerous member parties and encourage similar parties to merge together to produce a few solid parties, what I call “representative parties” that represent the wide spectrum of ideas highlighted by the opposition. The relationship between the council of the single United Front and the leaderships of each member parties needs to be defined in a way that will maximize the advantage of having the unity in the first place. For example, the single United Front should be the sole contact point for national, Diaspora, and international relations. The Diaspora should not splinter itself into membership in specific parties. Having the single United Front reach the Diaspora and the international community, and coordinate the non-violent struggle on a national level in Ethiopia unleashes the potent power that resides in a genuine unity. Such a strategy is the bedrock for the endurance of the unity. India had Gandhi, South Africa had Mandela, and the USA had King to spearhead the non-violent struggle. Why does Ethiopia not have a clear single championing leader for the cause of the opposition? Is it because we all want to lead but not follow? Is our personal agenda in the way to form a genuine unity? Enough is enough, it’s time to let destiny find the leader now. Here are some minimum qualifications, I think you should consider, when you look for this leader. First, he/she should be from the new generation. Time has changed, and the political tide has turned. The time is up for the old guard to continue being the front-runner. Pass the mantle and cheer from behind. Second, he/ she should be impartial to the member parties by not holding any leadership office at member party level. Third, he/she should be a tested, humble leader who has a heart to listen to the people and to put Ethiopia first.

Continued on page 24


TZTA: Page 23 : October 23, 2012: www.tzta.ca

Ethiopian community well represented at Mosaic Fest

Danforth Mosaic BIA sponsored the Mosaic Music Fest, Sat. Sept 29th, 2012 at Robertson Parkette, featuring 19 performers including Sebseb Belu Ethiopian Cultural Group.

services to browse.

Michael feels that “Residents and merchants from the Ethiopian community should be encouraged to value participation in these kinds of events. They are essential for the community. They help us come together and have a voice in local issues”. Toronto city government funds our Danforth Mosaic BIA so that our streets are beautified by flowers in summer and sparkle with winter holiday decorations. The BIA makes efforts to clean-up graffiti and street litter, so that visitors’ experience of the Danforth will be pleasant and comfortable. Michael and Banchi are working hard for the Ethiopian community as BIA Board members. Representation on the BIA leads to participation in city processes that are essential to advance acceptance and enhance promotion of the concept of “Little Ethiopia” on the Danforth.

City Councillor, Jane with board Members of BIA Among the Ethiopian members of Danforth Mosaic BIA present were Board members, Michael Kidus, Dukem Restaurantand Banchi Kinde, Rendezvous Restaurant. On behalf of the BIA, both Michael and Banchi acknowledged City Councillors, Janet Davis, Ward 31, Paula Fletcher, Ward 30, Mary Fragedakis, Ward 29,Mary-Margaret McMahon,Ward 32, who attended the Fest. The councilors expressed their appreciation of the rich contribution that the Ethiopian community has made to life on the Danforth. The Councilors’ comments addressed the fact that Ethiopian businesses form a vibrant segment of the commercial community, inhabiting one of the newest and longest BIA's in Toronto. Danforth Mosaic BIA extends along an area of 2.9 km. and stretches along the Danforth from Westlake Avenue on the east to Jones Avenue on the west, giving residents and visitors a choice of more than 400 shops and

What is a BIA? “Simply put, a Business Improvement Area (BIA) is an association of commercial/industrial property owners and tenants within a specified district who join together with official approval of the City in a self-help program aimed at stimulating business”. For more info http://www.toronto.ca/bia/ danforth_mosaic.htm

Afternoon Tea with the Consul General

Consul General, Jim Dickmeyer makes remarks to Toronto’s Diaspora journalists at his residence during afternoon tea.

27 September 2012: Consul General, Jim Dickmeyer makes remarks to Toronto’s Diaspora journalists at his residence during afternoon tea. Leading journalists from Toronto’s Diaspora communities gathered on September 27th at the Consul General’s residence for an afternoon of baklava, cookies, and tea. True to Toronto’s vibrant multicultural societies – the journalists came from nations as diverse as Iran, El Salvador, Pakistan, Japan, Nepal, India, Russia and Ethiopia. All guests had the opportunity to mingle with Consulate staff including the new Consul General, Jim Dickmeyer. The journalists also had the opportunity to meet one another. Ideas were exchanged as

often as business cards, as the media professionals discussed their respective publications. Freelance Iranian-Canadian journalist, Mohammad-Bagher Samimi, spent the afternoon chatting with Nobuo Iromoto from the Nikka Times, an online Japanese-Canadian publication. Maria Vorobieva from Ethnic Channels Group noted, “It was good to greet my colleagues from various media outlets in such intimate and friendly settings.” The Consul General made brief remarks welcoming the guests, and praising their work in the community. With more than half of Toronto’s population born outside of Canada, the Diaspora media serve as vital channels of communications throughout the country’s immigrant communities.


TZTA: Page 24: October 23, 2012: www.tzta.ca

There's a Hollywood Growing in Africa by Samuel Bekele

Just a month ago, the Toronto Film Festival hosted one of its most successful and unique event in recent memory.

makers an international destination to partner and take advantage of an influential booming industry that shows promise.

The well-attended event hosted Hollywood movies as well as featured movies made in Asia via a unique initiative called Asian Film Festival. For TIFF -- it's a catch up to what has been a phenomenal Asian film industry that continues to show popularity and growth worldwide.

As TIFF moves forward with its noble growth of a true international destination, I hope it will also recognize African filmmaking that is also emerging all over the world. The African Diaspora as well as Africans in Africa is increasingly captivated by their own movie making and it's slowly becoming just as popular as Hollywood films.

TIFF hopes to capture the essence of Toronto's diversity in people and as "Toronto is uniquely placed to be a part of the conversation about that change because of our population, our audience here and how outward-looking we are." With the new Asian initiative, TIFF hopes to offer financiers, actors, filmmakers and policy

In Canada as well as in the United States, African filmmakers are bringing their stories to a large audience. For instance -- Wondwossen Dikran is collaborating with noted African and North American filmmakers to produce a movie about an America tourist who travels to Kenya in Mzungu.

After Three Strikes, Rob Anders Should Be Out by Samuel Bekele

In Canada, five non-citizen individuals have been honoured with an honorary Canadian citizenship and three have been Nobel Peace Prize laureates.

The first to be honored was former Swedish diplomat and Holocaust hero, Raoul Wallenberg in 1985 followed by former South African President, Nelson Mandela in 2001. Since then, Tenzin Gvatso, the 14th Dalai Lama, Aung San Suu Kyi, the once Prime Ministerelect of Burma and His Highness, the Aga Khan, the 49th Imam of the Shia Ismaili Muslims have been honored with Canada's highest honor to a non citizen. In the years Canada honoured these distinguished citizens, the act was accepted by the House of Commons unanimously except in 2001. This was the year Nelson Mandela was honoured by Parliament on his rare state visit to Canada. The act was accepted by the then five recognized political parties in the House of Commons yet failed to get an unanimous support. This was because of one certain parliamentarian, Rob Anders, who became the sole member to vote against the act calling Mandela a "criminal and a communist." This was not only an embarrassment to his political party and his then party leader, Preston Manning but was a black eye for Canada and its reputation. Earlier today, in a published article in iPolitics, Anders commented about the life of the late NDP Leader, Jack Layton and his illness that intimately took his life. He remarked how: "I actually think one of the great stories that was missed by journalists was that Mr. Mulcair, with his arm twisted behind the scenes, helped to hasten Jack Layton's death." He further stated: It was very clear to me watching the two of those gentlemen in the front benches, that Jack Layton was ill and that Mr. Mulcair was making it quite obvious that if Jack wasn't well enough to fight the campaign and fight the election that Continued from page 22

he should step aside, and that because of that, Mr. Layton put his life at risk to go into the national election, and fight it, and did obviously an amazing job considering his state of health, and that he did that partly because of the armtwisting behind the scenes by Mulcair and then subsequently died. The Prime Minister reacted on twitter via his Director of Communications by remarking how "Mr. Anders' comments regarding Jack Layton in no way represent the views of Prime Minister Harper or the Government."

Mzungu is an African term for white people is the title of a new movie that is on the works by a collaboration of African born filmmakers from North America. Inspired by actual events, Mzungu (pronounced [muh-zun-gooo]) is about an American traveler's nightmarish vacation in Kenya after waking up from a night of hard partying to accusations of committing a grisly murder. In unexpected scenario, he is forced to see life from the perspective of a local Kenyan with all its shortcomings. At its core, the movie touches on human relationships, a flawed system of justice, and the cultural boundaries that affect everyone who's ever traveled to a foreign country. For Wondwossen Dikran, "It's a story that must be told...I knew after reading the script that I had to get involved because I had never seen or heard anything like it, and here came opportunity to be able to tell this unique story in an unfiltered and unmasked manner." It's an ambitious story that will captivate and move African movie-making forward. It's an organic story told from an African perspective by ambitious movie makers.

made unless the producers come up with seed money to give it its foundation. That is the reality of most African moviemaking. For the movie to be a reality, it also needs the same support and guidance that was afforded to Asian filmmakers. The team behind the film has turned to the crowd funding circuit via Kickstarter as a viable alternative to the traditional financing methods of the Hollywood studio system. Actor Matthew Lillard (The Descendants) and writer/ director Paul Schrader (Auto Focus) showcased their projects online though Kickstarter.com and independently each raised over $150,000 from fan contributions. African movies are no different than that of Asian. They need to be nurtured not out of petty but as an investment. African movies are rare. They are art, organic and a human experience that is rarely told especially from an African perspective. Let us give it a foundation and celebrate it. It just might be a worthwhile investment. TIFF, are you listening? Follow Samuel Getachew on Twitter: www. twitter.com/GetachewS

The Mzungu movie, for instance, will not be

For Rob Anders -- controversy is nothing new. He was once removed from a veteran's affairs committee for frequently falling asleep and showing disrespect for our veterans. On Monday, it was Nova Scotia NDP MP who spoke eloquently about Rob Anders and how the Prime Minister should act instead of sending a mere Twitter statement condemning a hurtful statement from a person who holds such a distinguished public position. He commented in part how "If I was Mr. Harper, he would be gone, out of the Conservative Party in a heartbeat. That kind of attitude, that kind of comment, that's insane. That is a disgrace to not only Mr. Mulcair but to the legacy of Mr. Layton. Think about how Olivia Chow must feel. That is just absolutely cold-hearted ......he should be removed from Parliament altogether." Even though I believe the electors are ultimately responsible in making judgment to their local MPs, I believe the Prime Minister should act and remove him from the Conservative Party of Canada immediately. While the moderates in our political parties excite, unite and inspire us, the extremists worry and disturb us passionately as much. Rob Anders is not just an embarrassment to his political party but to Canada and the public service as a whole. Extremism and stupidity should have no place in our Canadian public discourse. Follow Samuel Getachew on Twitter: www. twitter.com/GetachewS

The first requirement alone would exclude several of the current opposition leaders. Would they still be excited to get on with this program now that they are out of the limelight? Let your action speak louder than just your talk: are you in it for yourself, or for Ethiopia?

lead the way in abandoning the drama and ushering the real thing into the political space. Such an act cannot allow the government to play the drama as usual but face reality head on. The real power has nothing to do with having military force, but having eternal ideals that touch humanity now and forever. That chance is equally available for both the government and the opposition.

The creation of the single United Front and a few representative parties should progress in time with much deliberation. A quick fix during election season has no place for this kind of serious dream act. The time to start is today, not tomorrow. Here is what seems to be an impossible mission. You know that this is the will of the people. The people like to believe that you have what it takes to accept this challenge. You have the capacity to show that we are one big intelligent family that specializes in making the impossible possible.

At the moment, the ball is neither in the government’s court nor in the opposition’s court. The real engagement in the democratic motion has not yet begun. The ball is sitting idle in the middle, while the two groups are preoccupied with their own respective obsession to be right at either extreme polar end. Time will tell who will assume the higher moral ground and lead Ethiopia into democracy and prosperity instead of being mired in the status quo. This is an independent voice of truth in love.

In conclusion, the opposition has the opportunity to

The writer can be reached at (Z@myEthiopia.com)

KANG ELECTRONICE The Lowest prices in Town

55-LCD TV

SALE

$599.99

LCD-TV-32...............$199.99

LCD-TV-2HCH..........$139.99

LCD-TV-42...............$249.99 TV-UGCLO...............$399.99 DVD.........................$14.99

DVD Player

DVD+VCR.................$49.99 TV-13-LCD-HD..........$94.99 TV-17-LCD-HD..........$79.99 DVD-7.6....................$29.99 DVD-9.C....................$79.99 DVD-10-C..................$99.99 TV-7HD.....................$69.99 JVC-460W.................$199.99 55-LED-TV.................$599.99 24-LCD-TV.................$129.99 SONY-3D-1000W.......$199.99


TZTA: Page 25: October 23, 2012: www.tzta.ca

A

DENTAL Hygiene Clinic

*WITH NEW PATIENT EXAM AND CLEANING

COMPLETE FAMILY DENTAL CARE General Dentistry Crowns and Bridges Orthodontic Treatment Root Canal Dentures Night Guards Full Dental Cleaning

All Insurance Plans Accepted Including ODSP and OW Call or visit us to book an appointment: 1920 Weston Road Unit 218 B

(647) 620 – 5444 www.aedentalhygiene.com


TZTA: Page 26 : October 23, 2012: www.tzta.ca

10 YEARS ANNIVERSARY


TZTA:Page 27: October 23, 2012 www.tzta.ca

Just Listed

SOLD !!

Leading Edge Realty Inc; Brokerage Each Office independtly Owned and Operated.

በአዲስ፡ግንባታ፡ላይ፡ያለ፡ቤትም፡ወይም፡ ኮንዶሚኒየም፡በቶሮንቶና፡አካባቢው፡ለመግዛት፡ ካሰቡ፡ወይም፡ዕቅድዎ፡ውስጥ፡ካለ፡ከመወሰንዎ፡ በፊት፡በሙያው፡ልምድን፡ያካበተውን፡መስፍንን፡ 416-877-7421 ደውለው፡ያነጋግሩ።የብሮከር፡ ፓኬጅ፡ይኖረናል። በአነስተኛ፡ተቀማጭ፡ቤት፡መግዛት፡ስትችሉ፡ ለምን፡በኪራይ፡ቤት፡ይኖራሉ?...በበለጠ፡ ለመረዳት፡416-877-7421፡ደውለው፡መስፍንን፡ ያነጋግሩ።መፍትሔ፡ይኖረዋል።

Just Listed

MESFIN BEKELE

የቤትዎን፡ግምት፡ማወቅ፡ይፈልጋሉ?፡በነጻ፡ ግምቱን፡አቀርብልዎታለሁ።

Sales Representative

Bus. (416)686-1500 Direct:

(416) 877-7421 Fax: (416) 386-0777

SOLD !!

416-876-5023

FAX:-

(800)479-4101

820 MarkhamRoad, Scarborough ON

OFFICE

Not intended to solicit under the contract

Licenced under the Ministry of College and Universities

Tel:-416-430-0909 Cell:-

2010

E-mail: mbekele@rockketmail.com www..c21leadingedge.com

S O L D !!

THIS ISSUE: VOLUME XVII, NO. 5: April 24, 2012 / NEXT ISSUE: TUESDAY, May 22, 2012 / NEXT ADVERTISEMENT& DEADLINE: May 17, 2012

TORONTO VARIETY STORE

ቶሮንቶ ቫራይቲ ስቶር

96 Simington Ave. Toronto ለመጀመሪያ ጊዜ በሲሚንግተንና በብሉር አካባቢ የቶሮንቶ ቫራይቲ ስቶር ተከፍቶላችኋልና ኑና ጎብኙን! ስልክ ደውሉልን! የምትፈልጉትን ትገበያላችሁ፤ ጠቅለል ባለ ሁኔታ የሚከተሉት ለምስሌ ይኖረል። 1. ፍረሽ አትክልትና ፍራፍሬ ይህ ልዩ ያደርገናል። 2. ቅመማ ቅመም፣ እንጀራ፣ 3. ልዩ ልዩ የግሮሰሪ ሸቀጦች፣ ኮሊንግ ካርድ፣ 4. ሌላም ሌላም...

Ethnic Press discusses issues of concern with Liberal Leader...

The tragedy of Afewerk Tekle’s death...More page 17

The young and gifted Ethiopian artist Tewodrose Kassahun (AKA Teddy Afro)...More page 20

More page 18

We sell all sorts of variety items, spices, phone card, Video, C.D. D.V.D. Fruit, Flower and more... Tel:-

416-516-7458

ታሪካዊ የዋልድባ ገዳም ውድመት ይቁም! ገጽ 3 እና 14 ይመልከቱ Your Total Auto Service Centre more than just mufflers

ከአሁን በኋላ መኪናዎ ላይ ለሚደርሱ ችግሮች ስፒዲ ጋራዥ በብርምፕተን ተከፍቶልዎታል። We give all services

አቶ ወርቁ መኮንን

Mufflers & Exhaust Systems Auto repairs, brakes, installation, tires etc...

9 Fisherman Drive, Brampton ON L7A 2X9 Tel:- 905-840-9965 * Fax:- 905-840-9531 Woru Mekonnen (Owner/Manager) We are ready to serve you Mondayto Saturday. Please drop by and see us anytime no appointments necessary

Ethic cleansing is an emotion arousing act of violation against civilians ...More page 21

MACELLERIA SAN GABRIELE ቅዱስ ገብርኤል ሥጋ ቤት 416-654-5440

PERSONAL SUPPORT WORKER DIPLOMA PROGRAM

7 ቀን ከሰኝ እስክ እሁድ ክፍት ነን።

416-691-1500

ለቁርጥ፣ ለክትፎ፣ ለጥብስ፣ ለወጥ ለመሳሰሉት ትኩስና ንፁሕ ሥጋ በፈለጋችሁት መጠን አናቀርባለን። ለሠርግ፣ ለልደት፣ ለማንኛውም ዝክርና ድግስ ሙሉ በግና በሬ ቢያዙንም በርዎ ድረስ አንኳኩተን እናስረክብዎታለን።

Tel:-416-743-5111

Global Immigration Services

ግሎባሊሚግሬሽን አገልግሎት 828C Bloor Ste. W.

998 St. Clair Ave, W. Toronto (Oakwood & St. Clair)

Cell Phone:-

416-574-4900

Fax:- 416-538-2297

E-mail:- berhanet53@yahoo.ca

Commissioner of Oath

ፊውቸር አካዳሚ ኦፍ ኸልዝ ኬር በአጭር ጊዜ በጤና ሙያ ሥልጠና በመሥጠት ወደ ሥራ ያሰማራል።

WORLDWIDE TRAVEL When planning your tripc call us first @

416-535-8872

Toronto, ON M6G 1M2 Office phone:- 416-537-4800

- Citizenship Application - Appeals - Refugee cases - Detention Reviews - Sponserships - Live in care giver - Pre Removal and Humaniterian Cases

851 Bloor Street West, Toronto, ON

በኛ በኩል ስትሄዱ ፀሐይ ለፀሐይ ነው መንገዱ።

Reg. # 464--2328

ቶሮንቶ ሜዲካል ሰፕላይ ሊትድ የሕክማና ቁሳቁሶች ለሽያጭ የሚያቀርብ ነው።

* ማንኛውም በኤሌትሪክና በእጅ የሚነዱ ዌል ቼሮች * ባለ ሶስትና አራት ጎማ እስኩተር * ባለ አራት ጎማ ዋከር መንቀሳቀሻ ለሚያስፈልገው በክስዎ 0% (በነፃ) እስከቤትዎ ድረድ እናማጣልዎታለን። * በተጨማሪም እነዚህን ቁሳቁሶች ከሁሉም በቀነሰ ዋጋ እናቀርባለን። * የመታጠቢያ ቤት ለደህንነት፣ ለጥንቃቄ የሚያስፈልግዎትን እቃዎች * የሆስፒታል ዓይነት አልጋዎች ከነ ቁሳቁሶቹ * በስፖርትም ሆነ በሥራ ለተጎዱት የጥንቃቄ ማሸጊያ ቁሳቁሶችን እናቀርባለን * እንሹራንስም ሆነ የመንግሥት ክፍያውን እኛው አጠናቀን ፋይል እናደርግልዎታለን። ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ የሚያስፈልግዎ የሕክምና ቁሳቁሶዎችን እናቀርባለን፤ የምላክበትንም ጥንቃቄና ስልቱን እናሳይዎታለን፤ መጥተው ይጎብኙን።

Futures Academy of Healthcare is currently focusing on three main courses that we feel are in demand in our healthcare system today.

Personal Support Worker This is a caregiver who assists with daily personal care needs to persons who are dealing with the effects of aging, injury or other illness. The Personal Support Worker is usually guided by a Registered Nurse (RN) or a Registered Practical Nurse (RPN).It also includes First Aid & CPR courses.

English as a second language English as a Second Language for Adults (ESL) offers specialty ESL classes and provides English language programs.

Tel:

ይኸውም 1ኛ/ለግለቦች እርዳታ መስጠት፣ 2ኛ/ የመጀመሪያ እርዳትና 3ኛ/ ሲፒአር የመሳሰሉትን ኮርስ በመውሰድ በሆስፒታል፣ ለረጅም ጊዜ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው፣ ለአዛውንቶች፣ ለነርሲንግ ሆም፣ በጥሮታ ለሚኖሩ፣ ለደንበኞች፣ በአንድ ላይ ለሚኖሩ፣ ትምህርት ቤቶች ለመሳሰሉት የሥፍራ ቦታውች ለመቀጠር እድል ይሰጣል። ትምህርት ሲጨርሱ ዲፕሎም ይሰጣል። በተለይ ለመረዳት ስልክ ደውሉልን።

The Executive Group Joyce Lennon-Ewers has been involved in the healthcare industry for over 30 years. She has worked in public hospitals and nursing homes and has many years of teaching healthcare under her belt. With a B.Sc.N degree in Nursing and an BA from York University, Joyce brings a wealth of experience to Futures Academy.

416.653-1010 * F: 416.653.1012

Contact Us Today:

944 St. Clair Avenue West, Unit B Toronto, ON M6C 1C8 CANADA

info@futureacadamyof healthcare.com * http://www.futuresacademyofhealthcare.com


TZTA:Page 28: October 23, 2012 www.tzta.ca


Issuu converts static files into: digital portfolios, online yearbooks, online catalogs, digital photo albums and more. Sign up and create your flipbook.